የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ በተለያዩ ሰብሎች ከተሸፈነው መሬት 5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል

May 30, 2025

IDOPRESS

አዶላ፤ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፦በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ በተለያዩ ሰብሎች ከተሸፈነው መሬት 5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ይጠበቃል የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡


በዞኑ በልግ አብቃይ በሆኑ 6 ወረዳዎች ከ250 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር ተሸፍኖ እየለማ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡


በጉጂ ዞን በየአመቱ ከመጋቢት 15 እስከ ሚያዝያ መጨረሻ የዝናብና የበልግ አዝመራ የዘር ወቅት እንደሆነም ተገልጿል፡፡


የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ ቂልጣ ጂማ በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 245 ሺህ 398 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡


አጠቃላይ ከታቀደውም በ13 ሺህ በላይ ብልጫ በማሳየት 258 ሺህ 671 ሄክታር መሬት በአምስት ዋና ዋና ሰብሎች በዘር ተሸፍኗል፡፡


በልማቱም ከ280 ሺህ የሚበልጡ አርሶ አደሮች መሳተፋቸውን አቶ ቂልጣ አስታውቀዋል።


በዘንድሮ የበልግ አዝመራ ከለማው ከዚሁ መሬት ከ5 ነጥብ 8 ሚሊዮን ኩንታል አጠቃላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡


በጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ በበኩላቸው፥ ምርታማነትን ለማሳደግ የተመቻቸው አዳዲስ አሰራር የስራ መነሳሳት ፈጥሯል ብለዋል፡፡


ከእነዚህም የኩታ ገጠም፣የመስመርና የትራክተር አስተራረስ ዘዴ የምርጥ ዘርና የተሟላ የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ዋና ዋናዎቹ እንደሆኑ ጠቅሰዋል፡፡


ለዘንድሮ በልግ ከተዘጋጀው ውስጥ 107 ሺህ ሄክታሩ በመስመር፤ 164 ሺህ ሄክታር መሬት ደግሞ በኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ እየለማ ነው ብለዋል፡፡


በልማቱ ከተሳተፉት መካከል የአዶላ ሬዴ፣የዋደራ፣ የሰባቦሩ፣ የግርጃ፣ የአጋ ወዩና ሻኪሶ ወረዳ አርሶ አደሮችም አዳዲሶቹን አሰራሮች በመከተል እያለሙ ይገኛሉ ብለዋል፡፡


በአዳዲስ አሰራር ከለማው ከዚሁ መሬት ውስጥ ከበቆሎ፤ስንዴና ቦለቄ ሰብሎች ከፍተኛ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል፡፡


ለስራው ስኬታማነት ከ95 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያና 37 ሺህ 334 ኩንታል ምርጥ ዘር ጥቅም ላይ መዋሉን አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026