
ሀዋሳ፤ግንቦት 20/2017( ኢዜአ)፦በሀዋሳ ከተማ እየተገነባ ያለው ሁለተኛው ምእራፍ የ5 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ በመገባደድ ላይ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፤ የሁለተኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ስራ ያለበትን ደረጃ እና አጠቃላይ ክንውኑን ተመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፥የልማት ስራዎችን መጀመር ብቻ ሳይሆን በጥራትና በፍጥነት የማጠናቀቅ ልምድ እየዳበረ መጥቷል።
አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፥ ግንባታው በተያዘለት ጊዜ በጥራትና በፍጥነት በመገባደድ ላይ ይገኛል ብለዋል።
የግንባታው ስኬት የክልሉ መንግስት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና የከተማው ህዝብ የትብብርና እገዛ ድምር ውጤት መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ በተለገሳት ተፈጥሮና በነዋሪዎቿ ብርቱ ጥረት እድገቷና ውበቷ ይበልጥ እየፈካ መሆኑን ተናግረው፥ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግራት ይሆናል ብለዋል።
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መኩሪያ መርሻዬ፥የመጀመሪያው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ በጥራትና በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱን አንስተዋል።
የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ደግሞ በጥራትና በፍጥነት በተሻለ መልኩ በመከናወን ላይ መሆኑን ጠቁመው፥በአጭር ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ብለዋል።
የፕሮጀክቱን አፈፃፀም በጥራትና በተሻለ ፍጥነት ለማጠናቀቅ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የድጋፍና የክትትል ሥራውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
የግንባታ ስራውን እያከናወነ ያለው ይርጋዓለም ኮንስትራክሽን ባለቤት ኢንጂነር ዘላለም ወልደአማኑኤል፥የፕሮጀክት ሥራው በጥራትና በፍጥነት ሌት ከቀን እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የግንባታ ስራው የኮንክሪት አስፋልት፣ የፍሳሽ፣ የእግረኛና ብስክሌት መንገድ፣ የአረንጓዴ ልማትና ሌሎችም ከተማዋን የሚያዘምኑ እና የሚያስውቡ ስራዎችን ያካተተ መሆኑን ጠቁመው፥በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቅ መሆኑን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026