የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኤሌክትሮኒክስ የምክረ ሀሳብ መስጫ ስርዓት በረቂቅ ህጎች የዝግጅት ሂደት የዜጎችን ተሳትፎ የሚያሳድግ ነው-አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ

May 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 20/2017(ኢዜአ)፦ኤሌክትሮኒክስ የህዝብ ምክረ ሀሳብ መስጫና መቀበያ ስርዓት በረቂቅ ህጎች የዝግጅት ሂደት የዜጎችን ተሳትፎ በማሳደግ ግልፅና ጠንካራ ህጎችን ለማውጣት እንደሚያስችል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ተናገሩ።


ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት በረቂቅ ህግ ላይ ሃሳብ እና አስተያየት የሚሰጡበት ኤሌክትሮኒክስ ወይም የበይነ መረብ የህዝብ ምክረ ሀሳብ መስጫ ስርዓት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።


በመርኃ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያስላሴ እና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።


የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ እንደገለጹት፥ መንግስት የፍትህ ዘርፉ ውጤታማ እንዲሆን በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።


በፍትህ ስርዓቱ የህዝብና የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲያድግ እና እንዲጠናከር በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።


ዛሬ ይፋ የሆነው ኤሌክትሮኒክስ የምክረ ሀሳብ መስጫ ስርዓት በህግ ዝግጅት ላይ የህዝብ ተሳትፎ እንዲያድግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ብለዋል።


የአሰራር ስርዓቱ ዜጎች በአካል መገኘት ሳይጠበቅባቸው ባሉበት ሆነው በረቂቅ ህጎች ላይ ሃሳባቸውን እንዲሰጡ እድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰዋል።


የተዘረጋው አሰራር ከህግ አኳያ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ በቴክኖሎጂ ልማት እየተከናወኑ የሚገኙ ውጤታማ ተግባራትን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል።


የመንግስት ተቋማት ህጎችን በሚያዘጋጁበት ወቅት የአሰራር ስርዓቱን መሰረት በማድረግ ዜጎች በአግባቡ እንዲሳተፉ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።


የፍትህ ሚኒስትር ሀና አርዓያስላሴ በበኩላቸው፥ ለህግ የበላይነት መስፈን የህግ ጥራትን፣ተገማችነትን፣ወጥነትንና ተደራሽነትን ማሳደግ ቀዳሚ ጉዳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ለዚህ ደግሞ በህግ ማርቀቅ ሂደት ላይ ዜጎችን በማሳተፍ ሰፊ ምክክር ማድረግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።


ከዚህ አንጻር የተዘረጋው ኤሌክትሮኒክስ የምክረ ሀሳብ መስጫ ስርዓት ሰፊ ተደራሽነት ለመፍጠር፣ተሳትፎን ለማበረታታትና ግልጽነትን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።


ስርዓቱ በክልል ደረጃ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የለማ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሯ፥ በህግ አወጣጥ የተሻለ ቅንጅት ለመፍጠርና ወጥነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።


#Ethiopian_News_Agency


#ኢዜአ


#Ethiopia

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026