
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 18/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ዘላቂና አካታች የፋይናንስና የኢንሹራንስ ስርዓትን ለመገንባት ትልቅ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለፁ።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ድርጅት ዓመታዊ ኮንፍረንስ እና ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በብዙ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ሪፎርም እየተከናወነ ነው።

ብድርን በተመለከተ ያሉ ችግሮች ሲፈቱ የኢንሹራንስ ዘርፉን በሚፈለገው አቅም ማሳደግ እንደሚቻልም ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የኢኮኖሚ ሪፎርም የግሉን ዘርፍ በሚያበረታታና ኢንቨስትመንትን በሚያረጋግጥ መልኩ በልዩ አመራር እየተተገበረ መሆኑን አንስተዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ በፋይናንስ ዘርፉ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገትን የሚያረጋግጥ ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳየ ነውም ብለዋል።
በፋይናንስ ዘርፉ ህግ ከማሻሻል ጀምሮ በኢኮኖሚው ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ የሚያመጡ የአሰራር ሪፎርሞች መከናወናቸውን ጨምረው ተናግረዋል።

ባለፉት የለውጥ ዓመታት በፋይናንስ ዘርፉ የተሰሩ አጠቃላይ ስራዎች የኢንሹራንስ ዘርፉን ዕድገት በማገዝ በኩል ሰፊ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የዲጂታል ሽግግር በአጠቃላይ ኢኮኖሚያዊ ለውጥን ለማምጣትና የኢንሹራንስ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አበርክቶ እንዳለውም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026