የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ የሚውል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ እየተደረገ ነው - የክልሉ ግብርና ቢሮ

May 21, 2025

IDOPRESS

ግንቦት፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለመኸር እርሻ ጥቅም ላይ የሚውል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ እንዲደርስ እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮ ኃላፊው ጌቱ ገመቹ እንደገለጹት፣ ለመኸር እርሻ መደበኛ ኮምፖስትን ጨምሮ የተለያዩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ ነው።

የተፈጥሮ ማዳበሪያ የአፈር ለምነትን ለመጨመርና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቅሰው፣ በበጀት ዓመቱ 250 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ መደበኛ ኮምፖስት እና 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ቫርሚ ኮምፖስት ተዘጋጅቶ ለአርሶ አደሩ እየተሰረጨ ነው።


በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከላት በመገንባት አርሶ አደሩ በዝግጅት ሂደቱ ግንዛቤውን የማሳደግ ሥራ መሰራቱንም ተናግረዋል።

በክልሉ የተፈጥሮ ማዳበሪያን ከማዘጋጀት ጎን ለጎን የአርሶ አደሩን የአፈር ማዳበሪያ ፍላጎትለሟሟላት በአሁኑ ወቅት ከ6 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ክልሉ ገብቶ ለአርሶ አደሩ እየተሰራጨ መሆኑንም ገለጸዋል።


በቡኖ በዴሌ ዞን በተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጃ ማዕከል የአፈር ለምነት ባለሙያ መሃመድ ሱልጣን፤ ቫርሚ ኮምፖስት የአፈርን ለምነት በመጠበቅ፣ የአፈር አሲዳማነትን በመቀነስና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።

ማዕከሉ ቫርሚ ኮምፖስት በማምረት ለአርሶ አደሩ ከማቅረብ ጎን ለጎን አርሶ አደሮችን በማሰልጠን የበኩሉን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በሚገኝ የቫርሚ ኮምፖስት ማምረቻ ማዕከል ውስጥ የምትሰራው ብርሃኔ ሶቦቅሳ፤ ማዕከሉ ቫርሚ ኮምፖስት አምርቶ በተመጣጣኝ ዋጋ ለአርሶ አደሮች እያቀረበ ይገኛል።

በተጨማሪ አርሶ አደሩ በራሱ በማምረት እንዴት መጠቀም እንደሚችል በማዕከሉ በኩል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጻለች።

የተፈጥሮ ማዳበሪያው የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ከመጨመረ ባለፈ የአፈር ማዳበሪያ ለመግዛት የሚያወጣውን ወጪ ቀንሶለታልም ነው ያለችው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026