የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ቢሮው ለኢንቨስትመንት ቦታ ወስደው ለዓመታት ሳያለሙ በቆዩ 96 ፕሮጀክቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ ወሰደ

May 19, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 8/2017 (ኢዜአ)፦የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ቦታ ወስደው ለዓመታት ሳያለሙ በቆዩ 96 ፕሮጀክቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።


የክልሉ መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በወላይታ ሶዶ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።


የቢሮው ኃላፊ ወይዘሮ አጸደ አይዛ፥ በከተማዋ ለኢንቨስትመንት ተብለው የተወሰዱ ቦታዎችን ሳያለሙ ማስቀመጥ እንደማይቻልና አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል።


የክልሉ መንግስት የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ፈጥነው ወደ ሥራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል ያደርጋል ብለዋል።


ይሁን እንጂ በክልሉ የወሰዱትን መሬት ሳያለሙ ለዓመታት አጥረው ባስቀመጡ 96 ፕሮጀክቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል።


ከእነዚህም መካከል 34 ፕሮጀክቶች ውላቸው እንዲቋረጥ የተደረገ ሲሆን ቀሪዎቹ ላይ የማስጠንቀቂያ እርምጃ የተወሰደ መሆኑን አስታውቀዋል።


የጉብኝቱ ዓላማ የሪጂዮ ፖሊ ከተሞችን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ለማሳደግ እና የባለሀብቶችን ጥያቄ ለመፍታት መሆኑን ገልፀው፥ ባለሀብቶች የሚያነሷቸውን ማነቆዎች በመፍታት ዘርፉን ለማነቃቃት ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልሉ በግብርናና በአገልግሎት እንዲሁም በኢንዱስትሪ ዘርፎች ከ1 ሺህ 700 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ስራ ላይ መሆናቸውንም ወይዘሮ አጸደ አመልክተዋል።


በክልሉ የኢንቨስትመንት ሥራዎችም ከ120 ሺህ በላይ ዜጉች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም ጠቁመዋል።


የክልሉ መንግስት እያከናወነ ያለውን የቁጥጥርና ክትትል እንዲሁም የድጋፍ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፥ ባለሀብቶች የወሰዱትን መሬት በገቡት ውል መሰረት በማልማት የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026