
አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በቡና ግብይት ስንሰለት እና በምርታማነት እድገት ላይ በተሰሩ ስራዎች ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ ማሳደግ መቻሉን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገለፁ።
በበጀት አመቱ 10 ወራት ወደ ውጭ ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፥ መንግስት የቡና ምርትና ምርታማነትን በመጨመርና ጥራቱን በማሻሻል በአለም ገበያ ተፎካካሪነትን ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው።
በዚህም በበጀት ዓመቱ አሥር ወራት 354 ሺህ ቶን ቡና በመላክ 1 ነጥብ 87 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡
ይህም በአገሪቱ የቡና የወጪ ንግድ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነ ከፍተኛ አፈጻጸም መመዝገቡን ነው ዳይሬክተሩ የተናገሩት።
አፈጻጸሙ ከባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በመጠን 145 ሺህ ቶን ጭማሪ ማሳየቱን ገልጸው፤ በገቢ ረገድም 870 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ የተመዘገበበት መሆኑንም ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።
ቡናን በስፋት መትከል፣ ያረጁ ቡናዎችን መጎንደልና ቡናን በብዛትና በጥራት ለማምረት አስችሏል ያሉት ዶክተር አዱኛ፤ በዚህም በሄክታር የሚገኘውን የቡና ምርት ማሳደግ መቻሉንና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳጠር ላይ የተሰራው ስራ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ማስቻሉንም ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት ከአመት አመት በመጠንም በጥራትም እየጨመረ እንዲመጣ ማድረጉን ገልፀዋል።
በበጀት አመቱ ቀሪ ወራቶችም ከቡና ንግድ ለማግኘት የታቀደውን 2 ቢሊዮን ዶላር ከግብ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026