
አዲስ አበባ፤ግንቦት10 /2017 (ኢዜአ)፦መዲናዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባዋ በአዲስ ዓለም ዓቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ (ETEX 2025) ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች በዚሁ ወቅት፤ ከተማዋ ከሀገር አልፎ የዓለም አቀፍ እና አህጉረ አቀፍ ኮንፈረንስ የማዘጋጀት አቅም እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

ባለፉት አስር ቀናት ብቻ የኮንፈረንስ እና ኤክስፖዎች በመዲናዋ መከናወናቸውን ገልፀው፤ ይህም የከተማዋን ገቢ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በሀገሪቱ በቴክኖሎጂ ልማት ላይ ትልቅ ለውጥ እና እድገት እየተመዘገበ ይገኛልም ብለዋል።
ከተማዋን ስማርት ሲቲ ለማድረግ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
"ኢቴክስ 2025" ኤክስፖ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ጫፍ ላይ መድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ 2025 በአዲስ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026