
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እየተገኙ ባሉ ውጤቶች ዓለም አቀፍ ድጋፍና ዕውቅና መገኘቱን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለጹ።
የኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም ዛሬ መካሄድ ጀምሯል።
የኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ በፋይናንስ ዘርፍ የተደረጉ ማሻሻያዎችና የተገኙ ውጤቶችን በፎረሙ ላይ አቅርበዋል።
በፋይናንስ ዘርፍ የተደረገው ማሻሻያ መነሻ፣ የማሻሻያውን ይዘት፣ የተገኙ ውጤቶችና ቀጣይ የዘርፉን እቅድ በዝርዝር አቅርበዋል።
የውጭና የሀገር ውሰጥ የብድር ጫና መጨመር፣ የዋጋ ግሽበትና ሌሎች ያስከተሉት የማክሮ ኢኮኖሚ አለመጣጣም ለማሻሻያው መነሻ እንደሆኑ አስታውሰዋል።

በማሻሻያው ትኩረት ከተደረገባቸው ነጥቦች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን ዘመናዊ ማዕከላዊ ባንክ የሚያደርጉ አሰራሮችን መዘርጋት፣ የዋጋ ግሽበትን መቆጣጠር፣ የፋይናንስ መረጋጋትን ማምጣት ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።
በማሻሻያው የፋይናንስ ዘርፉን በቴክኖሎጂ በመደገፍ አዳዲስ አሰራሮችና ገበያዎችን መፍጠር ተችሏል ነው ያሉት።
የውጭ ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰን መደረጉን ጠቅሰው፤ ለግል የውጭ ምንዛሬ ቢሮዎች ፈቃድ በመስጠት ወደ ስራ መግባታቸውንም አብራርተዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተደረገ በኋላ የተመዘገቡ ውጤቶችን የዘረዘሩት የባንኩ ገዥ፤ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት መጨመር፣ የዋጋ ግሽበት መቀነስ፣ በፋይናንስ ዘርፉ መረጋጋት መታየቱ ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተዋል።

የባንክ ዘርፉን ለዓለም አቀፍ ተቋማት ክፍት ማድረግ፣ በባንኮች መካከል ያለው ግብይት መጨመር እና መንግስት ከብሔራዊ ባንክ የሚወስደውን ብድር ዜሮ ማድረስ መቻሉንም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የተረጋጋ ምጣኔ ሃብት ለመፍጠር በወሰደችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያና እየተገኙ ባሉ ውጤቶች ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ሀገራት ድጋፍና እውቅና እያገኘች መሆኑን ተናግረዋል።
ለአብነትም የዓለም የገንዘብ ድርጅት፣ የዓለም ባንክ፣ ከቻይናና ሌሎች ሀገራት የእዳ መክፈያ እፎይታ ጊዜና የገንዘብ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
የዲጂታል ፋይናንስ ክፍያ፣ ተቀማጭ የውጭ ምንዛሬ መጠን መጨመር፣ የፋይናንስ አካታችነትና ሌሎች ቀጣይ በፋይናንስ ዘርፉ ትኩረት ከሚደረግባቸው ጉዳዮች መካከል መሆናቸውን ዘርዝረዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026