የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ ናቸው

May 15, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።

ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ በአሶሳ ከተማ እየተሰጠ ካለው የአመራሮች እና የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ስልጠና ጎን ለጎን በመደመር መጽሀፍ ገቢ እየተገነባ የሚገኘውን ሙዚየም፣ የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


ከጉብኝቱ በኋላም በመደመር መጽሀፍ እየተገነባ የሚገኘው ሙዚየም የክልሉን ህዝቦች ባህል እና እሴት የሚያንፀባርቅ እና ለትውልድ እንዲተላለፉ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል።

ፕሮጀክቱ የመደመርን ፅንሰ ሃሳብ በተግባር የሚያሳይ ለጥናት እና ምርምር የሚያገለግል የብልጽግና እሳቤ ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመሆኑም በክልሉ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች የሀገርን ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና ለማረጋገጥ የሚያግዙ መሆናቸውን ተናግረዋል።


የግንባታ ሂደቱ 90 በመቶ የደርሰው ሙዚየሙ የቅርሶች ማስቀመጫ፣ ቤተመጻህፍት፣ ቴአትር ቤት እንዲሁም በክልሉ የሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦች መገለጫዎችን የያዘ መሆኑን አንስተው እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማትም የከተማዋን ገጽታ የሚቀይር እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ነው ያሉት።

የኮሪደር ልማት በሁሉም አካባቢዎች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ መሆኑን አንስተው የከተሞች ዕድገት እና ዘመናዊነት ለኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ መሠረት የሚያኖር መሆኑንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026