የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ ድጋፍ ወሳኝ ነው

May 15, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።

ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በደብረ ብርሃን ከተማ ለሀይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የኮምፒዩተርና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ እገዛና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።


በዚህ ረገድ ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ ለትምህርት ቤቱ ላደረገው እገዛ ምስጋናቸውን አቅርበው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ ለዲጅታል ዘርፉ እድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

የተደረገው ድጋፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂን ለትምህርት ጥራትና ውጤታማነት በመጠቀም ወጣቶችን በእውቀትና ክህሎት አንጾ ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑንም ተናግረዋል።

በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሪጅናል የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሲሳይ ዘሪሁን፤ ኩባንያው ለትምህርት ቤቱ የ14 ዘመናዊ ደስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች ድጋፍ ማድረጉን አንስተው ዓላማውም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ እውቀትን ለተማሪዎች ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።


በእለቱ ለትምህርት ቤቱ ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ በአካባቢው በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችም የእህልና ሌሎችም ምግብ ነክ ቁሳቁሶችን መለገሱ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026