
ደብረ ብርሃን፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ ድጋፍ ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ።
ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በደብረ ብርሃን ከተማ ለሀይለማሪያም ማሞ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የኮምፒዩተርና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ።
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ለማፋጠን በሚደረገው ጥረት የቴሌኮም ዘርፉ እገዛና ድጋፍ ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህ ረገድ ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ ለትምህርት ቤቱ ላደረገው እገዛ ምስጋናቸውን አቅርበው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ ለዲጅታል ዘርፉ እድገት ትልቅ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
የተደረገው ድጋፍ ዲጂታል ቴክኖሎጂን ለትምህርት ጥራትና ውጤታማነት በመጠቀም ወጣቶችን በእውቀትና ክህሎት አንጾ ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሪጅናል የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ሲሳይ ዘሪሁን፤ ኩባንያው ለትምህርት ቤቱ የ14 ዘመናዊ ደስክ ቶፕ ኮምፒዩተሮች ድጋፍ ማድረጉን አንስተው ዓላማውም የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ እውቀትን ለተማሪዎች ተደራሽ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።

በእለቱ ለትምህርት ቤቱ ከተደረገው ድጋፍ በተጨማሪ በአካባቢው በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ወገኖችም የእህልና ሌሎችም ምግብ ነክ ቁሳቁሶችን መለገሱ ታውቋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026