የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮች በጂኦፓርኮች እና ጂኦ ቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ እድገት ወሳኝ ነው - ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

May 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮች በጂኦፓርኮች እና ጂኦ ቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ እድገት ወሳኝ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ገለፁ።

ቱሪዝም ሚኒስቴር ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት(ዩኔስኮ) ጋር "የዩኔስኮ ዓለም አቀፍ ጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ለዘላቂ ልማት ያላቸው ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የዩኔስኮ የአፍሪካ ህብረት፣ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሸን እና የኢትዮጵያ ላይዘን ቢሮ ኃላፊ ሪታ ቢሶኖውት(ዶ/ር) እንዲሁም የፌዴራል ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊዎች፣ በዘርፉ የተሰማሩ የኢትዮጵያውያንና የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ባለሞያዎች ተገኝተዋል።

አውደ ጥናቱ በዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን አቅም ማሳደግ ጨምሮ የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክ ፕሮጀክቶችን በኢትዮጵያ እና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማስጀመር ያለመ ነው።

በተጨማሪም የጂኦፓርክን ጽንሰ ሃሳብ በአህጉሪቱ ማስተዋወቅ ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ መንግሥት ትኩረት ከሰጣቸው አምስት የኢኮኖሚ አውታሮች አንዱ ቱሪዝም ነው።

ዘርፉ የሚጠበቅበትን ያህል ለሀገር እድገት እንዲያበረክት እየተመራ እንዳለ አንስተው፤ ይህም በተሰጠው ትኩረት ልክ ያሉ እድሎችን ለማዳበር እና ለማስተዋወቅ አስተዋጽኦ ፈጥሯል ነው ያሉት።

አዲሱ ረቂቅ የቱሪዝም ፖሊሲ የጂኦቅርስ ቦታዎችን መጠበቅ፣ ጂኦፓርኮችን ማቋቋም እና የጂኦቱሪዝም አስፈላጊነት ላይ ትኩረት የሰጠ ነው ብለዋል።

የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ተዋናዮችን በጂኦፓርኮች እና ጂኦቱሪዝም ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ ለዘርፉ ዘላቂ ልማት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዛሬው መድረክም የዩኔስኮ ግሎባል ጂኦፓርክስ እና ጂኦቱሪዝም ጽንሰ ሀሳብን ለማስተዋወቅ ያግዛል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026