የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎች የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅት ሊጠናከር ይገባል

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎችን የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ገለጸ።


ባለሥልጣኑ ከህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የትብብርና የቅንጅት ስራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።


የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለስራቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ባለፉት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።


በዚህም የፖሊሲና ህግ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንና የተቋማት አቅም የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።


ይህንን ተከትሎ በተለይ ባለፉት የሪፎርም ዓመታት በርካታ ሲቪል ድርጅቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡


በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ ከስምንት ሺህ በላይ ድርጅቶች ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን፤ 60 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተመዘገቡ መሆናቸወን ገልጸዋል።


እንደ አቶ ፋሲካው ገለጻ፤ የትብብር ስራዎችን በተደራጀ ስርዓትና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው ዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር የማቀናጀት ስራ እየተሰራ ነው ።


የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትብብርና የቅንጅት መድረክ መቋቋሙንም አንስተዋል ።


ይህ ትብብር እና ቅንጅት የአገሪቷን ውስን ሀብት አጠቃቀም እንደሚያሻሽል፣የስራ መደራረብን እንደሚቀንስ እንዲሁም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያጎለብት ተናግረዋል።


ከዚህም በተጨማሪ የፋይናንስ፣የአቅምና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።


የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎች የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አቶ ፋሲካው ሞላ አስገንዝበዋል፡፡


የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፥ የተቋሙ ስልጣንና ተግባር በተመለከተ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመፍታት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።


በጥናት፣በትምህርትና ስልጠና ስራዎች ላይም ከድርጅቶቹ ጋር በጋራ ለመስራት ያስችላል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026