
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎችን የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ገለጸ።
ባለሥልጣኑ ከህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ጋር በመተባበር የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የትብብርና የቅንጅት ስራዎች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ አካሂዷል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ በወቅቱ እንደገለጹት፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለስራቸው ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ባለፉት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ስራዎች ተከናውነዋል።
በዚህም የፖሊሲና ህግ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንና የተቋማት አቅም የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን አንስተዋል።
ይህንን ተከትሎ በተለይ ባለፉት የሪፎርም ዓመታት በርካታ ሲቪል ድርጅቶች መመዝገባቸውን አስታውቀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ ከስምንት ሺህ በላይ ድርጅቶች ተመዝግበው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሲሆን፤ 60 በመቶ የሚሆኑት ባለፉት የሪፎርም ዓመታት የተመዘገቡ መሆናቸወን ገልጸዋል።
እንደ አቶ ፋሲካው ገለጻ፤ የትብብር ስራዎችን በተደራጀ ስርዓትና በዘላቂነት ለማስቀጠል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከሚመለከታቸው ዘርፍ መስሪያ ቤቶች ጋር የማቀናጀት ስራ እየተሰራ ነው ።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣንና የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የትብብርና የቅንጅት መድረክ መቋቋሙንም አንስተዋል ።
ይህ ትብብር እና ቅንጅት የአገሪቷን ውስን ሀብት አጠቃቀም እንደሚያሻሽል፣የስራ መደራረብን እንደሚቀንስ እንዲሁም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት እንደሚያጎለብት ተናግረዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የፋይናንስ፣የአቅምና ሌሎች ችግሮችን ለመፍታት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።
የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ ስራዎች የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ቅንጅታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባም አቶ ፋሲካው ሞላ አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ዋና እንባ ጠባቂ ስመኝ ውቤ በበኩላቸው፥ የተቋሙ ስልጣንና ተግባር በተመለከተ ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመፍታት ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ጉልህ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
በጥናት፣በትምህርትና ስልጠና ስራዎች ላይም ከድርጅቶቹ ጋር በጋራ ለመስራት ያስችላል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026