
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 24/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በክህሎት ልማት ሁለተኛውን የአርበኝነት ምዕራፍ መጀመሯን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።
ኢትዮ ክህሎት አራተኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ ከሚያዚያ 27 እስከ ግንቦት 2 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርኃ ግብሩን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
ሚኒስትሯ በመግለጫቸው፤ ኢትዮ ክህሎት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የስልጠና ጥራትን ለማረጋገጥ በየሁለት ዓመቱ የሚካሄድ መሆኑን ተናግረዋል።
መርኃ ግብሩ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ሲካሄድ በቆየው ውድድር አሸናፊ የሆኑ ወጣቶች የሚሳተፉበት የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር መሆኑን አስታውቀዋል።
የክህሎት ውድድሩ ከኢትዮጵያ ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ እና ከገበያው ፍላጎት ጋር የሚያስተሳስሩ ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሚያተኩር መሆኑን ጠቁመዋል።
ውድድሩ በ22 ዘርፎች እንደሚካሄድና የቱሪዝም ዘርፉን ማነቃቃት የሚያስችል መርኃ ግብር መሆኑን ነው ያስረዱት።
መርኃ ግብሩ ኢትዮጵያን በዘርፉ ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር ተወዳዳሪ እንደሚያደርጋት ጠቁመው፣ በውድድሩ 70 አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች ለእይታ ይቀርባሉ ብለዋል።
የውድድሩ ዓላማ የተሻሉ ቴክኖሎጂዎችን በማበልጸግ ከገበያው ጋር ማስተሳሰር መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡
በ2016 በጀት ዓመት 81 ቴክኖሎጂዎች መልማታቸውንና በዘንድሮው በጀት ዓመት ደግሞ 180 ተሳታፊዎች 99 ቴክኖሎጂዎች በማልማት ሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ሁለተኛውን የአርበኝነት ምዕራፍ ጀምራለች ያሉት ሚኒስትሯ፤ የክህሎት ውድድሩ የኢትዮጵያን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026