
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና የቻይና የባህል እና የቋንቋ ልውውጥ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ የፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ገለጹ።
የቻይና ቋንቋ ቀን በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) በበዓሉ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የቻይና ቋንቋ ቀን በተቋሙ መከበር የሀገራቱን ባህሎች ለመተዋወቅ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ እና የቻይና የባህል እና የቋንቋ ልውውጥ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግርን ለማሳለጥ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።
ቋንቋ ሰዎችን፣ ባህልንና ጥበብን የሚያገናኝ ድልድይ መሆኑንም ጨምረው አመላክተዋል።
እንደ ኮንፊሺየስ የሙያ ትምህርት ተቋም ያሉ የቻይና ቋንቋ ማዕከላት መቋቋማቸው በሁለቱ ሀገራት በባህል፣ ሳይንስና ስነ ጥበብ መካከል ያለውን የጋራ ግንዛቤ ማሳደግ የሚያስችል ተጨማሪ እድል እንደሚፈጥር ጠቁመዋል።
በአሁኑ ጊዜ በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በሌሎች ዘርፎች ካለው ጠቀሜታ የተነሳ የቻይና ቋንቋን የመማር ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ተናግረዋል።
በየዓመቱ ተመራቂዎች የቻይና ቋንቋን እንደ ተጨማሪ ትምህርት በተቋሙ እንዲማሩ እንደሚደረግም አመላከተዋል።
በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ የባህል አማካሪ ዣንግ ያዌ በበኩላቸው የቻይና ቋንቋ ቀን መከበሩ በቻይና ቋንቋ የተካተተውን ታሪክና ባህል ብቻ ሳይሆን መግባባትና አብሮ መኖርን የሚያበረታታ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያና ቻይና በተለያዩ ዘርፎች ያላቸውን የረጅም ጊዜ የሁለትዮሽ ትብብር ጠንካራ መሆኑን ገልጸዋል።
የቋንቋ ልውውጥ በሁለቱ ሀገራት ህዝቦች መካከል ባህሎች እንዲራመዱ እና ጥልቀት እንዲኖራቸው እንደሚያደርግ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በተለያዩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ትብብርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ቻይና ቁርጠኛ መሆኗንም አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026