
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦በመዲናዋ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 124 የተለያዩ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለጸ።
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የፕሮጀክቶች ክትትልና ድጋፍ ዳይሬክተር ብሩክ ተሆነ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ በመዲናዋ በርካታ ኢንቨስትመንትን የሚያበረታቱ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
በመዲናዋ ባለፉት ጥቂት አመታት የተገነቡ የኮሪደር፣ የቱሪዝም መሰረተ ልማቶችና መዳረሻዎች እንዲሁም ሌሎች የልማት ስራዎች ኢንቨስትመንቱ እንዲያድግ እያስቻሉ ነው ብለዋል።
በከተማዋ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ በመሆኑም በተለይ በቱሪዝምና ሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች ለመሰማራት በርካታ ባለሀብቶች ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኮሚሽኑ ይህን ታሳቢ በማድረግ የኢንቨስትመንት ፍቃድ በተቀላጠፈ ሁኔታ ከመስጠት በተጨማሪ ፍቃድ የወሰዱ ባለሀብቶች በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገቡ ድጋፍና ክትትል እያደረገ መሆኑን አንስተዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን፣ በትምህርት፣ በጤና፣ በአይሲቲ፣ በማኑፋክቸሪንግና በአገልግሎት ዘርፎች 124 ፕሮጀክቶች ወደ ስራ መግባታቸውን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ከአስር ሺህ በላይ ለሆኑ ነዋሪዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን ተናግረዋል፡፡
የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በፍጥነት ወደ ተግባር መግባት ለከተማዋ ኢኮኖሚ ትልቅ ሚና እየተወጣ መሆኑንም አንስተዋል።
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፥ኮሚሽኑ አገልግሎቱን ለማዘመን ዲጂታላይዜሽን ላይ ውጤታማ ተግባራትን በማከናወን የኢንቨስትመንት ጉዳዮችን በቀላሉ በኦንላይን መፈጸም እንዲቻል አድርጓል፡፡
ከተማ አስተዳደሩ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን በማንሳት፥ ባለሀብቶች በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026