
አሶሳ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ ለትንሳዔ በዓል የተሻለ የፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና ነጋዴዎች ተናገሩ።
ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአሶሳ ከተማ ያለውን የግብይት ሁኔታ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።
በወቅቱ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እና ነጋዴዎች እንደተናገሩት የፍጆታ ዕቃዎች እና የቁም እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ እንዳለ ገልጸዋል።

ዱቄት፣ ዘይት እና ሌሎች ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ ዕቃዎችን ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ ዓለሙ እንዳሉት በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሻለ አቅርቦት አለ ብለዋል።
ይለፉ አበዛ የተባሉ የአትክልት እና ፍራፍሬ ነጋዴ በበኩላቸው ሽንኩርት በአካባቢው በስፋት በመመረቱ አቅርቦት ላይ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።
በተመሳሳይ የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦትም በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።

በአሶሳ ከተማ የቁም እንስሳት ገበያ ማዕከል ያገኘናቸው ሸማች አቶ ስሜነህ ተፈራ የእርድ ሰንጋዎች ከሌላው ጊዜ በተሻለ መግባቱንና ሰው እንደየፍላጎቱ ግብይት እየፈጸመ መሆኑን አንስተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም ነጋዴዎች የፍጆታ ዕቃዎችን በበቂ ሁኔታ እንዲያቀርቡ የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።
ህብረተሰቡ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀጥታ ከአምራቹ እንዲያገኝ በማድረግ የበዓል ገበያው የተረጋጋ እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቁም እንስሳት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በእርባታ እና በማድለብ ስራ የተሰማሩ አካላት ምርታቸውን ወደ ገበያ እንዲያቀርቡ ተደርጓል ነው ያሉት።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026