የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በአሶሳ ከተማ የተሻለ የበዓል ፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት አለ - ሸማቾች እና ነጋዴዎች

Apr 21, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሚያዝያ 10/2017(ኢዜአ):- በአሶሳ ከተማ ለትንሳዔ በዓል የተሻለ የፍጆታ ቁሳቁስና የእርድ እንስሳት አቅርቦት መኖሩን ሸማቾች እና ነጋዴዎች ተናገሩ።

ኢዜአ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአሶሳ ከተማ ያለውን የግብይት ሁኔታ ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

በወቅቱ አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ሸማቾች እና ነጋዴዎች እንደተናገሩት የፍጆታ ዕቃዎች እና የቁም እንስሳት አቅርቦት በበቂ ሁኔታ እንዳለ ገልጸዋል።


ዱቄት፣ ዘይት እና ሌሎች ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ ዕቃዎችን ሲሸምቱ ያገኘናቸው ወይዘሮ ሙሉ ዓለሙ እንዳሉት በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሻለ አቅርቦት አለ ብለዋል።

ይለፉ አበዛ የተባሉ የአትክልት እና ፍራፍሬ ነጋዴ በበኩላቸው ሽንኩርት በአካባቢው በስፋት በመመረቱ አቅርቦት ላይ ችግር እንደሌለ ጠቁመዋል።

በተመሳሳይ የቁም እንስሳት ግብይት አቅርቦትም በተሻለ ሁኔታ መኖሩንና መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን ሸማቾች ተናግረዋል።


በአሶሳ ከተማ የቁም እንስሳት ገበያ ማዕከል ያገኘናቸው ሸማች አቶ ስሜነህ ተፈራ የእርድ ሰንጋዎች ከሌላው ጊዜ በተሻለ መግባቱንና ሰው እንደየፍላጎቱ ግብይት እየፈጸመ መሆኑን አንስተዋል።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አስር ኢብራሂም ነጋዴዎች የፍጆታ ዕቃዎችን በበቂ ሁኔታ እንዲያቀርቡ የቅድመ ዝግጅት ስራ መከናወኑን ተናግረዋል።

ህብረተሰቡ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀጥታ ከአምራቹ እንዲያገኝ በማድረግ የበዓል ገበያው የተረጋጋ እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።


በቁም እንስሳት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች በእርባታ እና በማድለብ ስራ የተሰማሩ አካላት ምርታቸውን ወደ ገበያ እንዲያቀርቡ ተደርጓል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026