
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 9/2017(ኢዜአ)፡- በውጭ ምንዛሬ ጨረታው አንድ ዶላር በአማካይ 131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገለጸ።
ባንኩ ዛሬ ያደረገውን የ70 ሚሊዮን ዶላር ጨረታ ውጤት ይፋ አድርጓል።
አንድ ዶላር በአማካይ በ131 ነጥብ 4961 ብር መሸጡንና በጨረታው ላይ የተሳተፉ 26 ባንኮች የውጭ ምንዛሬውን መውሰዳቸውን ገልጿል።
በዛሬው ጨረታ በተሸጠው ዶላር የባንኮቹን 96 በመቶ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት/ጥያቄ በአጥጋቢ ሁኔታ ምላሽ መስጠት መቻሉን አመልክቷል።
ብሔራዊ ባንክ ቀጣይ የውጭ ምንዛሬ ጨረታውን ከሁለት ሳምንት በኋላ ያካሂዳል።

ባንኩ ጨረታው የሚያካሂድበት ቀን እና ሰዓት ጨረታው ከመካሄዱ ከአንድ ቀን በፊት አስቀድሞ እንደሚያሳውቅም ገልጿል።
ጨረታው በማዕከላዊ ባንክ እየተከማቸ ካለው የውጭ ምንዛሪ የተወሰነውን መጠን ለግሉ ዘርፍ ለማቅረብና የባንኩን የገንዘብ ፖሊሲ ዓላማ ለማሳካት እንደሚረዳ ተገልጿል።
በተጨማሪም ጨረታው የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና ሪፎርሙ ከተጀመረ ወዲህ መሻሻል እያሳየ የመጣውን የውጭ ክፍያ ሚዛን በይበልጥ ለማጠናከር እንደሚያግዝም ነው ባንኩ ያመለከተው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026