
ሀዋሳ፤ሚያዝያ 6/2017 (ኢዜአ) :- በሲዳማ ክልል ከ29 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ መዘጋጀቱን የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን አስታወቀ ፡፡
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ ለኢዜአ እንደተናገሩት ከ32 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኝ ለማዘጋጀት ታቅዶ እስካሁን ከ29 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ችግኝ ማዘጋጀት ተችሏል፡፡
በ4 ሺህ 500 ሄክታር ላይ አዲስ ቡናን ለመትከል ከጥር ወር ጀምሮ የችግኝ መትከያ ጉድጓዶች መቆፈራቸውንና በያዝነው ወር ተከላው እንደሚጀመር ጠቅሰዋል፡፡
የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ለቡና ተክል አስፈላጊውን እንክብካቤ የማድረግ እንዲሁም ያረጁና ምርት የማይሰጡ ቡናዎችን በመጎንደልና ነቅሎ በአዲስ የመተካት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በጉንደላና ነቅሎ በመተካት ሥራ ባለፈው ዓመት 8 ሺህ ሄክታር ማሳ ማደስ እንደተቻለ የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፥ በዚህ ዓመት ደግሞ 11 ሺህ 500 ሄክታር ማሳ መታደሱን ገልጸዋል፡፡
ቡና ከሚሰጠው ጠቀሜታው አንጻር በልዩ ትኩረት እየለማ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ የአለታ ወንዶ ወረዳ አርሶ አደር እንዳሻው ዩሬ ለዘንድሮ 1 ሺህ 500 ችግኝ ለመትከል ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን ገልፀዋል፡፡
አዲስ የሚተክሉት የቡና ችግኝ ዝርያቸው የተሻሻለ መሆኑን ጠቅሰው ከተተከለ በሁለት ዓመት ውስጥ ፍሬ መስጠት እንደሚጀምር አስረድተዋል፡፡
የዚሁ ወረዳ አርሶ አደር አየለ ቡናራ፤ አምና 1 ሺህ 500 የቡና ችግኝ መትከላቸውን ገልፀው ዘንድሮሞ ከ 1 ሺህ 700 በላይ ችግኞችን ለመትከል የጉድጓድና ችግኝ ዝግጅት ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ለሚተክሉት የቡና ችግኝ በቂ የሆነ የተፈጥሮ ማዳበሪያ በማዘጋጀት እንደሚጠቀሙ የተናገሩት አርሶ አደር አየለ በመካከሉም የጥላ ዛፎችን እንደሚተክሉ አስረድተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026