የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች ስኬታማ አፈጻጸም ተመዝግቧል- ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ(ዶ/ር)

Apr 14, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካቾች ስኬታማ አፈጻጸም መመዝገቡን የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) አስታወቁ።

የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀን አፈጻጸም እና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተገምግሟል።


በመድረኩ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) የማክሮ ኢኮኖሚና የዘርፎች አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል።

የሁለተኛው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ የዘርፎች ምርታማነትና ተወዳዳሪነት ማጠናከር፣ የኢንቨስትመንት ንግድን ከባቢ ማሳደግ እንዲሁም የመንግስት የመፈጸም አቅምን ማጎልበት ዓላማ አድርጎ ወደ ትግበራ መግባቱን አብራርተዋል።

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በአራቱም ምሶሶዎች የተሻለ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰው፤ ይህም የስምንት ነጥብ አራት በመቶ የኢኮኖሚ እድገት ለማስዝገብ የተያዘው እቅድ እንደሚሳካ ያመላከተ ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ ኢንቨስትመንትና ቁጠባ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት ያላቸው ድርሻ መሻሻሉንም ነው የጠቀሱት።

ኢንቨስትመንት ከሀገር ውስጥ ጥቅል ምርት አኳያ ባለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከነበረበት 20 ነጥብ 5 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉን አንስተዋል።

የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብ ላይ የተሻለ አፈጻጻም መመዝገቡን የተናገሩት ሚኒስትሯ፤ የውጭ ብድር ጫና ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ያለውን ምጣኔ ወደ 13 ነጥብ 7 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የኢኮኖሚ እድገትን ከማሳላጡ ባሻገር ሦስት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ዶላር የእዳ ሽግሽግ ይዞ መምጣቱንም ተናግረዋል።

በሸቀጦችና የአገልግሎት ወጪ ንግድ የተሻለ አፈጻጸም መኖሩንም ሚኒስትሯ አብራርተዋል።

በሪፎርም ስራው በእዳ ውስጥ የነበሩ የመንግስት የልማት ድርጅቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ስራ ወደ ትርፋማነት መሸጋገራቸውንም ገልጸዋል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት መንግስት ምንም ዓይነት ብድር ከብሔራዊ ባንክ አለመውሰዱን ጠቅሰው፤ ይህም የዋጋ ንረቱን ለማረጋጋት ትልቅ ፋይዳ ማበርከቱን አብራርተዋል።

በሌላ በኩል መንግስት የኑሮ ውድነቱ በዜጎች ላይ ጫና እንዳያሳድር ለሴፍትኔት፣ ለመሰረታዊ ፍጆታ፣ ለነዳጅና ሌሎች ስትራቴጂክ ምርቶች የሚያደርገውን ድጎማ አጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።

ለአብነትም ለአፈር ማዳበሪያ ብቻ 62 ቢሊዮን ብር ድጎማ መደረጉን ነው የተናገሩት ።

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ፣ በውጭ እና በርቀት የስራ እድል ፈጠራ ውጤታማ ስራ መከናወኑንም ሚኒስትሯ ባቀረቡት ሪፖርት ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026