
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።
ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።
አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።
በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 የቢዝነስ ፎረም ግንቦት 4 እና 5 በአዲስ አበባ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ 2025 ከፍተኛ የቢዝነስ ፎረም በመጪው ግንቦት 4 እና 5 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ተገለጸ።
ፎረሙን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) እንደተናገሩት፥ የቢዝነስ ፎረሙ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች የተዘጋጀ ነው።
ለ3ኛ ጊዜ የሚካሄደው በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ የቢዝነስ ፎረም ኢትዮጵያን ከአፍሪካ ተቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ከማድረግ ባለፈ ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ገልፀዋል።
አዳዲስ ኢንቨስትመንትን መሳብ፣መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ማሳየት እና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማሳወቅ የፎረሙ ዓላማ ነው ብለዋል።
በፎረሙ የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዋቂ ኩባንያዎች፣የንግዱ ማህበረሰብ መሪዎች፣የፖሊሲ አውጪዎች፣አማካሪዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ እንደሚሳተፉም ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026