
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ):-የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የጀመራቸውን አበረታች ስራዎች አጠናክሮ እንዲቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ያስሚን ወሀብረቢ አሳሰቡ።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ዕቅድ አፈፃፀምና ቀጣይ ስራዎች ላይ ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።
ማህበሩ የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አዲስ የማህበሩን ፕሬዝዳንትና 11 የቦርድ አባላትን ምርጫ ማካሄዱ የሚታወስ ነው።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ያስሚን ወሀብረቢ ከጠቅላላ ጉባኤው በኋላ በተከናወኑ ስራዎች ዙሪያ ከማህበሩ አመራሮችና ከቦርዱ አባላት ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ ማህበሩ ሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች ባሳተፈ መልኩ የኢትዮጵያን ነጋዴ ሴቶች ለማብቃትና በንግዱ ዘርፍ በሴት ነጋዴዎች ላይ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል ነው ብለዋል።
ማህበሩ ባለፉት ጥቂት ወራት አበረታች ስራዎች ማከናወኑን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኢትዮጵያ ለሚካሄደው የኮሜሳ የሴት ነጋዴዎች የቢዝነስ ኮንፍረንስና ኤግዚቢሽን የዝግጅት ስራ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በቀጣይም በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተደራሽነትን በማስፋትና ገቢ የሚያመነጩ ስራዎችን በማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ነጋዴ ሴቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወይዘሮ በረከት ወርቁ በማህበሩ የተከናወኑ ስራዎችን አስመልክቶ ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026