
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 2/2017 (ኢዜአ)፡-በወላይታ ሶዶ ከተማ የተከናወነው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ውበት ከማጉላት ባለፈ በርካታ ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ።
አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች እንደገለጹት የኮሪደር ልማቱ ከተማን ውብ፣ ፅዱ እና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሯል።

የከተማው ነዋሪ ወጣት ዎጋሶ ጌታ የኮሪደር ልማት ከመካሄዱ በፊት በከተማዋ በርካታ ስፍራዎች ላይ ቆሻሻ በዘፈቀደ ስለሚጣል ለመጥፎ ጠረን በመዳረግ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸውን አዳጋች አድርጎት እንደነበር አስታውሷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የከተማ አስተዳደሩ የከተማዋን ነዋሪዎች በማስተባበር እያከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተማዋን ገጽታና ውበት ከማጉላት ባለፈ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር የጎላ አስተዋጾ እያበረከተ መሆኑን ተናግሯል።

በከተማው ከ40 ዓመት በላይ እንደኖሩ የገለጹት ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ወይዘሮ ከበቡሽ ዳኛቸው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም የነበሩ የከተማዋ መንገዶች ጠባብ እና በነጻነት ለመንቀሳቀስ ምቹ እንዳልነበሩ አስታውሰዋል።
በከተማው የኮሪደር ልማት በመጀመሩ ይህ ችግር መፈታቱንና የትራፊክ አደጋና መሰል ስጋቶችንም አስወግዶልናል ብለዋል ።

መንገዶቹ ከመስፋታቸው ባለፈ ጽዱና ንጹህ መሆናቸው ለህሊና ዕረፍት የሚሰጥ ነው ያሉት ወይዘሮ ከበቡሽ፣ ህብረተሰቡም በኮሪደር በለማ የእግረኛ መንገድ ላይ በእግር የመጓዝ ባህሉ እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
በቀጣይም የኮሪደር ልማቱ በከተማዋ እንዲስፋፋ የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።
የኮሪደር ልማቱ አረንጓዴ ስፍራና የህዝብ መዝናኛንም እንዲያካትት መደረጉ ነዋሪዎችም ሆነ ወደ ከተማው የሚገቡ እንግዶች ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ እያገዘ ነው ያሉት ደግሞ መምህር ታረቀኝ በቀለ ናቸው።

በልማቱ የእግረኞችና የተሽከርካሪ መንገዶች መለየታቸው የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት በማድረግ በኩል ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም ተናግረዋል
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎቶች ጽህፈት ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ አስራት ሉንግሶ በበኩላቸው የከተማዋን ገጽታ የሚቀይሩና ተወዳዳሪና ምቹ የሚያደርጉ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በከተማው 100 መቶ ሚሊየን ብር በሚጠጋ ወጪ ከሰባት ኪሎ ሜትር በላይ የሚሸፍን የኮሪደር ልማት ተጠናቅቆ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል
የኮሪደር ልማት ኢንሼቲቭ የከተማዋን ገጽታ ከመቀየርና ከማስዋብ አንጻር ያለውን ፋይዳ ህብረተሰቡ በመረዳቱ ያደረገው ድጋፍና አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑንም አቶ አስራት ጠቅሰዋል።
ፕሮጀክቱ ከተማዋን ጽዱና ለኑሮ ምቹ ከማድረግ ባለፈ ከ300 ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የገለጹት አቶ አስራት፣ በከተማዋ የኮሪደር ልማቱን በማስፋፋት ከተማን ለማዘመንና ተወዳዳሪ ለማድረግ ጠንክረን እንሠራለን ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026