
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2 /2017(ኢዜአ)፦ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የአገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቋጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀምሯል።
የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት፥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰጠውን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተሰርተዋል፡፡
ዛሬ የተመረቀው ሲስተም የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎትን በማዘመን እና በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል፡፡
በዘርፉ የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጦችን ዲጂታል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ ሌሎች በዘርፉ ተግባራዊ የሚደረጉ ቴክኖሎጂዎችም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያዘምነው ሲስተም በተባለው ጊዜ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።
ኢንስቲትዩቱ የአገልግሎት አሰጣጦችን የሚያቀላጥፉና ችግሮችን የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን የማልማቱን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አቅም የመገንባት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የተመረቀው ሲስተም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያበለጸገው መሆኑ ተገልጿል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026