የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር)

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2 /2017(ኢዜአ)፦ዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን በማስፋፋት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የአገልግሎት አሠጣጥን የማዘመን ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጠል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡


የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የጭነት ትራንስፖርትን ለመቋጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል የተቀናጀ የትራንስፖርት አስተዳደር (IFTMS) ሲስተም አስጀምሯል።


የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በማስጀመሪያ ስነ-ስርአቱ ላይ እንደገለጹት፥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚሰጠውን የአገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለያዩ የሪፎርም ስራዎች ተሰርተዋል፡፡


ዛሬ የተመረቀው ሲስተም የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎትን በማዘመን እና በማቀላጠፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ገልጸዋል፡፡


በዘርፉ የሚሰጡ የአገልግሎት አሰጣጦችን ዲጂታል ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተው፤ ሌሎች በዘርፉ ተግባራዊ የሚደረጉ ቴክኖሎጂዎችም በቅርቡ ወደ ስራ እንደሚገቡ ጠቁመዋል፡፡


የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የትራንስፖርት አገልግሎትን የሚያዘምነው ሲስተም በተባለው ጊዜ መጠናቀቁን አስታውቀዋል።


ኢንስቲትዩቱ የአገልግሎት አሰጣጦችን የሚያቀላጥፉና ችግሮችን የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን የማልማቱን ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ አቅም የመገንባት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።


የተመረቀው ሲስተም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያበለጸገው መሆኑ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026