የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ኢትዮጵያ በ177ኛው የፋኦ የካውንስል ስብሰባ እየተሳተፈች ነው

Apr 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዛሬ በጣልያን ሮም በተጀመረው 177ኛው የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) የካውንስል ስብሰባ እየተሳተፈች ነው።

በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት፣ በዓለም የምግብ ፕሮግራም እና የዓለም አቀፉ የግብርና ልማት ፈንድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተጠሪ አምባሳደር ደሚቱ ሃምቢሳ በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል።

አምባሳደር ደሚቱ ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያከናወኑ ያሉትን ውጤታማ ስራና በዚሁ ረገድ እያጋጠማቸው ያለውን ፈተና አስመልክተው አፍሪካን ወክለው ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

በስብሰባው ፋኦ በስትራቴጂክ እቅዱ ላይ በመወያየት አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያጋጠማቸው ያለው ፈተና እና መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም ድንገተኛ አደጋ በሚያጋጥማቸው ወቅት አፋጣኝ ምላሽ መስጠት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል።

ስብሰባው እስከ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026