
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዛሬ በጣልያን ሮም በተጀመረው 177ኛው የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) የካውንስል ስብሰባ እየተሳተፈች ነው።
በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት፣ በዓለም የምግብ ፕሮግራም እና የዓለም አቀፉ የግብርና ልማት ፈንድ የኢትዮጵያ ቋሚ ተጠሪ አምባሳደር ደሚቱ ሃምቢሳ በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል።
አምባሳደር ደሚቱ ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያከናወኑ ያሉትን ውጤታማ ስራና በዚሁ ረገድ እያጋጠማቸው ያለውን ፈተና አስመልክተው አፍሪካን ወክለው ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
በስብሰባው ፋኦ በስትራቴጂክ እቅዱ ላይ በመወያየት አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ሀገራት የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ እያጋጠማቸው ያለው ፈተና እና መፍትሄዎቻቸው እንዲሁም ድንገተኛ አደጋ በሚያጋጥማቸው ወቅት አፋጣኝ ምላሽ መስጠት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ይመክራል።
ስብሰባው እስከ ሚያዚያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026