
ባህርዳር ፤መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በዲጅታል ቴክኖሎጂ የተደገፈ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ።
በህዝብ የተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባከናወናቸው ተግባራት ላይ ከዳኞችና ተገልጋዮች ጋር በዛሬው እለት ውይይት አካሂዷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወይዘሮ እፀገነት መንግስቱ፤ በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ እየተሰጠ ያለው የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ የሚበረታታ መሆኑን አንስተው በተጠናከረ መልኩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የፍትህ ዘርፉን ፈጣን፣ ግልጽ፣ ተአማኒና ሚዛናዊነቱ የተጠበቀ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት የድጂታል አሰራሮችን ማስፋትና ማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህ ረገድ በአማራ ክልል የተጀመሩ ጥረቶችና እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ብለዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ጉብኝትም የሀገሪቱን የፍትህ ትራንስፎርሜሽን መርሃ-ግብር አተገባበር ለመገምገም መሆኑን ገልጸዋል።
የዳኝነት አካላት የለውጥ ፍኖተ ካርታ አፈጻጸም ለመመልከትና አፈጻጸሙን ከተገልጋዩ በመረዳት ግብረመልሶችን በመቀበል ለቀጣይ ስራ አቅጣጫ ለማመላከት መሆኑንም አስረድተዋል።
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህንጻ የእድሳት ሂደት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ጠቁመው ይህም ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026