
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 11/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት በአፍሪካ ትልቁን አየር መንገድ ለመገንባት በርካታ ሥራዎች እያከናወነች መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው።
በማብራሪያቸውም፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን ቁጥር፣ በመዳረሻ ብዛት ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ አየር መንገዶችን አስመርቆ ሥራ በማስጀመር እና የበረራ ድግግሞሽን በማሳደግ አገልግሎቱንና ትርፋማነቱን ጨምሯል ብለዋል፡፡
የዲዛይንና የፋይናንስ ጉዳዮች ሲጠናቀቁ ሥራው እንደሚጀመር ገልጸው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በፋይናንስ አቅሙ ከታላቁ የህዳሴ ግድብ የማይተናነስ ሀገራዊ ስትራቴጂክ ፕሮጀክት መሆኑን አንስተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ተጨማሪ መርከቦችን በማስገባት ሥራውን ለማዘመንና ትርፋማነቱን ለማረጋገጥ ጥረት እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የባቡር ትራንስፖርት አፈፃፀም ከአምናው ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ መጨመሩንና የዲጂታል ግብይት ከእጥፍ በላይ ማደጉን ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ የተጀመረው የካፒታል ገበያ ለአምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ፈቃድ መስጠቱን አንስተው፤ የዲጂታል ግብይቱና የንግድ ስርዓቱ በዚያው ልክ እየዘመነ የሚሄድበትን እድል ፈጥሯል ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026