የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ሶስተኛው የአፍሪካ የማዕድን ፎረም ዛሬ ይጀመራል

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።

ፎረሙ የሚካሄደው “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።

የአፍሪካ ህብረት ልዩ ኤጀንሲ የሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል ፎረሙን አዘጋጅቷል።

ፎረሙ በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ እክሎችን መፍታት እና እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ከአፍሪካ ህብረት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ባህላዊ የማዕድን ማውጣት ዘዴን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መተካት፣ ወደ ከባቢ አየር የሚገባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማምጣት የሚያስችሉ መንገዶች ላይም ውይይት እንደሚደረግ አመልክቷል።

በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።

የማዕድን ሀብት ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ትኩረት የሚሹ የህብረተስብ ክፍሎችን አቅም መገንባት እና ድምጻቸው እንዲሰማ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።

በፎረሙ ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።

ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026