
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- ሶስተኛው የአፍሪካ ማዕድን ፎረም በአፍሪካ ህብረት መቀመጫ አዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ ይካሄዳል።
ፎረሙ የሚካሄደው “የአፍሪካ የማዕድን ራዕይ ስኬቶች፣ ፈተናዎች እና እድሎች” በሚል መሪ ሀሳብ ነው።
የአፍሪካ ህብረት ልዩ ኤጀንሲ የሆነው የአፍሪካ ማዕድናት ልማት ማዕከል ፎረሙን አዘጋጅቷል።
ፎረሙ በማዕድን አስተዳደር፣ እሴት መጨመር እና ዘላቂነት ላይ የሚታዩ መዋቅራዊ እክሎችን መፍታት እና እድሎችን መጠቀም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንደሚመክር ከአፍሪካ ህብረት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ባህላዊ የማዕድን ማውጣት ዘዴን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መተካት፣ ወደ ከባቢ አየር የሚገባ የካርቦን ልቀትን መቀነስ እና ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ማምጣት የሚያስችሉ መንገዶች ላይም ውይይት እንደሚደረግ አመልክቷል።
በማዕድን መስክ ያሉ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ የትኩረት መስኮችን ከአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና እና አጀንዳ 2063 ጋር አጣጥሞ በማስኬድ ጠንካራ አጋርነት መፍጠር ሌላኛው የፎረሙ አጀንዳ ነው።
የማዕድን ሀብት ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ትኩረት የሚሹ የህብረተስብ ክፍሎችን አቅም መገንባት እና ድምጻቸው እንዲሰማ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ውይይት እንደሚደረግ ተጠቁሟል።
በፎረሙ ላይ የህብረቱ አባል ሀገራት፣ የማዕድን ዘርፍ ተዋንያን፣ የልማት አጋሮች እና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች ይሳተፋሉ።
ፎረሙ እስከ መጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የህብረቱ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026