
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 06/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ታዳጊዎችን በፈጠራና ቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማብቃት ያላትን ቁርጠኝነት የአሜሪካ ኤምባሲ አደነቀ።
አሜሪካ የመጪው ዘመን የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ መሪ ለሚሆኑት አፍሪካውያን ወጣቶች ድጋፍ እያደረገች መሆኗንም ጠቁመዋል።
በአሜሪካ ኤምባሲ የባህል ጉዳዮች ምክትል ኃላፊና በኢትዮጵያ የስፔስ ማዕከላት ዳይሬክተር ስትዋርት ዴቪስ እንደገለጹት፤ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግና ሂሳብ(ስቴም) አሜሪካ ድጋፍ ከምታደርግባቸው ዘርፎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ባሉ ስድስት የ'ስቴም' ማዕከላት በ'ስቴም'፣ ሮቦቲክስና ሌሎች ቴክኖሎጂ ዘርፎች ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልፀዋል።

የስቴም ማዕከላቱን ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በመቀሌ፣ ድሬዳዋና ጅማ መኖራቸውን ጠቁመው፤ በሃዋሳ ተጨማሪ ማዕከል ለመክፈት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሮቦቲክስ፣ ቴክኖሎጂና ሌሎች የፈጠራ ሃሳቦችን ለማበልፀግ የሚያስችሉ ስራዎች መሰራታቸውን አድንቀዋል።
በየጊዜው ወደ ማዕከላቱ የሚመጡ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር እያደገ መምጣቱን ጠቁመው፤ ይህም ታዳጊዎቹ ለመማርና ለመሻሻል ያላቸውን ፍላጎት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የሳይንስ ሙዚየምን ጨምሮ የታዳጊዎችን የፈጠራና ቴክኖሎጂ እውቀት ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ለዘርፉ ማደግ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል።
አሜሪካም አፍሪካውያን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም እንዲያወጡ ለማድረግ እገዛ እያደረገች መሆኗን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026