የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የወተት ምርት ጥራቱ ተጠብቆ ለሸማቹ በቀጥታ እንዲደርስ የገበያ ትስስር እየተመቻቸ ነው

Mar 15, 2025

IDOPRESS

ደብረ ብርሀን፤መጋቢት 5/2017(ኢዜአ) ፡-በአማራ ክልል እየተመረተ ያለውን ወተት ጥራቱ ተጠብቆ ለሸማቹ በቀጥታ እንዲደርስ የገበያ ትስስር እየተመቻቸ መሆኑን የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ገለጸ።

በቢሮው የእንስሳት ተዋጽኦ ግብይት ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ክንዴ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥ አርሶ አደሩ ወተትን በጥራትና በብዛት አምርቶ ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚነቱን እንዲያሳድግ እየተሰራ ነው።

በበጀት ዓመቱ ውስጥ 185 ሚሊዮን ሊትር ወትት በማምረት ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን ጠቅሰው፥ከታቀደው ውስጥ እስካሁን ከ83 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሊትር በላይ ወተት በማምረት ለገበያ ማቅረብ መቻሉን ገልጸዋል።

ለገበያ የቀረበው የወተት ምርትም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከሁለት ሚሊዮን ሊትር በላይ ብልጫ እንዳለው ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

በክልሉ የሚመረተውን ወተት ጥራትና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል የግብይት ቁጥጥር ስራው በህግ ማዕቀፍ እንዲመራ ለማድረግ ቢሮው እየሰራ ነው ብለዋል።

የወተት የግብይት ማዕከላትን በከተሞች በማቋቋም ምርቱ ከአምራቹ በቀጥታ ለሸማቹ ማህበረሰብ እንዲደርስ የሚያገናኝ የገበያ ትስስር የማመቻቸት ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም የምርት ጥራት መፈተሻ መሳሪያን በመጠቀም ጭምር እንደሆነ አመልክተዋል።

ወተት የሚያቀነባብሩ ፋብሪካዎችን በዩኔኖች፣ህብረት ስራ ማህበራትና ባለሃብቶች በስፋት ለማቋቋም አስፈላጊው እገዛ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

በደብረ ብርሃን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእስሳትና እንስሳት ተዋጽኦ ቡድን መሪ አቶ ዳዊት አሳምነው በበኩላቸው፥ ለሸማቹ የሚቀርብ የወተት ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ይህም በእንስሳት ጤና አጠባበቅ፣ አመጋገብና ንጽህና ላይ በማተኮር መሆኑን ገልጸዋል።

የደብረ ብርሃን ከተማ የወተት ግብይት ህብረት ስራ ማህበር አባል አቶ ለገሰ በጋሻው በሰጡት አስተያየት፥በማህበር መደራጀታችን የእንስሳት መኖ፣ ክትባትና ህክምና በተፋጠነ መንገድ እንድናገኝ አስችሎናል ብለዋል።

በዚህም የወተት ምርታማነትን በማሳደግ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በወተት ምርት ግብይት ላይ የተጀመረው የጥራት ቁጥጥር ፍትሃዊ ግብይትና ተጠቃሚነት እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ ሌላው አባል አርሶ አደር ግዛቸው ሸዋዬ ናቸው።

እሳቸውም በየቀኑ የወተት ምርት ለማህበራቸው በማቅረብ በዓመት ከ250 ሺህ ብር በላይ የተጣራ ትርፍ እንደሚያገኙ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026