
ቡታጅራ ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ) :-አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ትግበራ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ መሆኑ ተገለጸ።
ፖሊሲውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማስተዋወቅን ዓላማ ያደረገ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

በዚህ ወቅት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር እንዳመለከቱት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ለማጠናከርና የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደ አገር የተቀረጸው አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ፖሊሲው ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ገልጸዋል።
በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ነው፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026