የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የፖሊሲው ትግበራ ግብርናውን በማዘመን ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ ነው

Mar 13, 2025

IDOPRESS

ቡታጅራ ፤ መጋቢት 3/2017 (ኢዜአ) :-አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ትግበራ ዘርፉን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳው የላቀ መሆኑ ተገለጸ።

ፖሊሲውን በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማስተዋወቅን ዓላማ ያደረገ መድረክ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) እና የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ፋጤ ስርሞሎ በተገኙበት በቡታጅራ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡


በዚህ ወቅት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ስሩር እንዳመለከቱት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በስንዴ ልማት፣ በሌማት ትሩፋትና በሌሎችም ዘርፎች በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ተችሏል፡፡

በዘርፉ እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ለማጠናከርና የላቀ እመርታ ለማስመዝገብ እንደ አገር የተቀረጸው አዲሱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ በክልሉ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ፖሊሲው ግብርናን በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ ፋይዳ የላቀ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመድረኩ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እየተሳተፉ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026