
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ):- የስራ እና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ የኮሪያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ጁንግ ካንግ ጋር ዛሬ ተወያይተዋል።
ሚኒስትሯ ከአምባሳደር ጁንግ ጋር ኢትዮጵዮጵያ እና ኮሪያ ሪፐብሊክ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያና ኮሪያ ሪፐብሊክ ዘመናትን የተሻገረ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት እንደሆኑም አውስተዋል።
በውይይቱ በክህሎት ልማት እንዲሁም የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎች ላይ በትብብር ለመስራት ከመግባባት ላይ መደረሱን አመልክተዋል።
ኮሪያ ሪፐብሊክ በቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ለኢትዮጵያ ጠንካራ ድጋፍ ከሚያደርጉ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን ገልጸው ይህም ትብብሩን ወደ ላቀ ደረጃ ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
ሚኒስትሯ ለአምባሳደር ጁንግ የሀገራቱን የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት በማድረግ ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ላሳዩት ቁርጠኝነት ምስጋና አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026