
አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በስታርታአፕ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን ስነ-ምህዳር እየገነባች እንደምትገኝ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኮሪያ ዓለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ኮይካ) ጋር በመተባበር የስታርታፕ ዲጂታል አማራጭ ዲዛይን ምዕራፍ የተመለከተ አውደ ጥናት አካሄዷል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ፣ በኢትዮጵያ የኮሪያ ዓለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ያንግሺን ፓርክ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ማዕቀፉ የኢትዮጵያን የጀማሪ የስራ ፈጠራ (ስታርታፕ) ዘርፍ ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ማድረግ የሚያስችል ምቹ ስነ-ምህዳር መፍጠርን ያለመ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የስታርታፕ መድረክ ተወዳዳሪ ለማድረግ የሚያስችል ስነ-ምህዳር ለመገንባት እየሰራች እንደምትገኝ አመልክተዋል።
ስታርታፕ ፈጣን የሀገር ኢኮኖሚ ማበልፀጊያ ሞተር ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው የኢትዮጵያ ስታርታፕ ዲጂታል ፕላትፎርም ዘርፉን ለማሳደግ እና ኢኮኖሚውን የመደገፍ ፋይዳ አለው ብለዋል።
መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ብዙ ሀብት ማፍራት የቻሉ ወጣቶች እና ዜጎች ተፈጥረዋል ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው።
በኢትዮጵያ የኮሪያ አለም ዓቀፍ ተራድኦ ድርጅት ምክትል ዳይሬክተር ያንግሺን ፓርክ (ካይካ) ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ በስታርታፕ ዘርፍ ላይ የምታደርገውን የስነ-ምህዳር ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አመልክተዋል።
ኮይካ ኢትዮጵያ በዘርፉ ለምታከናውናቸው ስራዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026