የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ አስፋልት መንገድ ግንባታን ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ ነው

Mar 11, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ አስፋልት መንገድ ግንባታን በማፋጠን በጥራት አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት በቅንጅት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ።

የመንገዱ ግንባታ ያለበትን ሁኔታ የአማራ ክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራር አባላት ዛሬ ጎብኝተዋል።

በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ተስፋዬ አንተንይስሙ እንደገለጹት፤ የመንገዱን ግንባታ በጥራት በማከናወነ ለአገልግሎት ለማብቃት እየተሰራ ነው፡፡

ሆኖም የወሰን ማስከበር፣ የውሃ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ያጋጠሙ ጥቃቅን ክፍተቶችን ለማስተካከል የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ይህም ጥረት ከክልሉ፣ ከደቡብ ወሎ ዞንና ከአካባቢው አመራር አባላትና ህብረተሰቡ ጋር በመነጋገር መሆኑን አስረድተዋል፡፡


የሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት መንገድ የፕሮጀክት ተጠሪ መሃንዲስ ኢንጅነር ፀጋ ፈንታሁን በበኩላቸው፤ 74 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ግንባታ ሥራ ለማፋጠን በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የመንገዱ ግንባታ አጠቃላይ አፈጻጸም 39 በመቶ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ ግንባታው በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ እየተደረገ ባለው ጥረት የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር ጠይቀዋል።


የአማራ ክልል የርዕሰ መስተዳድሩ የመሰረት ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ በጉብኝቱ ላይ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚካሄዱ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ እየተሰራ ነው።

ከሐይቅ-ቢስቲማ-ጭፍራ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስር ለማጠናከር እንደሚያስችል ተናግረዋል።

ወሰን ማስከበርና ሌሎች ያጋጠሙ ጥቃቅን ክፍተቶችን ለማስተካከል እንደሚሰራም አስረድተዋል።


የአማራ ክልል መንገድ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ጋሻው አወቀ በበኩላቸው፤ የመንገዱ ግንባታ አፈጻጸም በተሻለ ሁኔታ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ግንባታው በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ህብረተሰቡ የበኩሉን ተሳትፎ እንዲያጠናክር መልዕክት አስተላልፈዋል።


ህብረተሰቡን በማወያየትና በማሳመን መንገዱ የሚያልፍበትን ቦታ ከሶስተኛ ወገን ነጻ በማድረግ የድርሻችንን እንወጣለን ያሉት ደግሞ የደቡብ ወሎ ዞን መንገድ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኢብራሂም ሐሰን ናቸው።

በጉብኝቱ የክልል፣ የደቡብ ወሎ ዞንና የሐይቅ ከተማ አመራር አባላትና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026