
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፦ የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ማሳደግ ላይ ያተኮረ ቀጣናዊ ኮንፍረንስ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ አራት ቀናት በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
ኮንፍረንሱ "የልማት ግቦችን ለመደገፍ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት" በሚል መሪ ሀሳብ እንደሚካሄድም ተጠቁሟል።
ኮንፍረንሱን የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(አይኤምኤፍ) እና የአይኤምኤፍ ቀጣናዊ የቴክኒክ ድጋፍ ማዕከል የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ(አፍሪታክ) በጋራ አዘጋጅተውታል።
በኮንፍረንሱ ላይ የኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር እና የገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ከ11 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የተወከሉ የዘርፉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የገቢና ፋይናንስ ባለሙያዎችና አማካሪዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙም በመረጃው ተመላክቷል።
የልማት ግቦችን መደገፍ የሚያስችልና የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከር የከንፍረንሱ ዋና ዓላማ መሆኑም እንዲሁ።
ቀጣናዊ ኮንፍረንሱ እስከ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ እና ከሁነቱ ጎን ለጎን የተሳታፊዎች የጉብኝት መርሃ ግብር እንደሚካሄድ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026