
ደሴ፤ መጋቢት 1/2017(ኢዜአ)፡- በደሴ ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ ገለፁ፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ ተጀምሯል፡፡

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደገለጹት በከተማው እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ እድገትና ለህዝቡ ተጠቃሚነት አዲስ ምዕራፍን የከፈተ ነው፡፡
የኮሪደር ልማት ግንባታውን በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለህዝብ ጥቅም ለማዋል ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ዛሬ መጀመሩ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡
የኮሪደር ልማት የብስክሌትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ ሌሎች መዝናኛ ሥፍራዎችን ያካተተ በመሆኑ ለጎብኚዎችና ለነዋሪዎች መዝናኛነት ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥር ገልጸዋል፡፡

በኮሪዳር ልማቱ የአካፋይ መንገድ፣ የመብራት ፖል ዝርጋታ፣ የካናል ስራ፣ የውሀ መስመር ዝርጋታና ሌሎች ተዛማጅ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ለልማቱ ህብረተሰቡ ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረገ መሆኑን ጠቁመው እስካሁን ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡
በደሴ ከተማ ከቧንቧ ውሃ-ሮቢት-ወሎ ባህል አምባ አንድ 1 አንድ 18 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክቷል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026