የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት እና አድዋ የአዲሱ ትውልድ የአንድነት መገለጫና የኩራት ምንጮች ናቸው - ጽህፈት ቤቱ</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት እና አድዋ የአዲሱ ትውልድ የአንድነት መገለጫና የኩራት ምንጮች መሆናቸውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የህዳሴ ግድብ በድህነት ላይ የተጎናጸፍነው ዳግም የዓድዋ ድል ነው ሲልም ጽህፈት ቤቱ አስታውቋል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ለ129ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

በመልዕክቱም ሁለተኛው የዘመናችን አድዋ የሆነው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት እና አድዋ የአዲሱ ትውልድ የአንድነት መገለጫና የኩራት ምንጮች ናቸው ብሏል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት እና አድዋ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን በአንድነት ለልማት ያስነሱ አርማዎች መሆናቸውንም አመልክቷል።

አባቶቻችን ሀገርን ለወራሪ ላለማስደፈር በዱርና በገደል በአርበኝነት ተፋልመው ሀገርን እንዳስከበሩ ሁሉ የአሁን ትውልድም አይደፈርም ብሏል።

በብድርና እርዳታ አይሰራም ተብሎ የሚታሰበውን አባይን ለማልማት በህብረት ተረባርቦ በማስጀመር፣ በመምራትና አሁን ለሚገኝበት ደረጃ ማድረስ የህዝቡ ትልቅ ድል መሆኑን ነው የገለጸው።

ከመላው ህዝብ እስከ እሁን ለህዳሴ ግድብ ከ21 ቢሊየን ብር በላይ የፋይናንስ ድጋፍ መሰብሰቡንና የግድቡ አጠቃላይ አፈጻጸም በአሁኑ ወቅት ከ98 በመቶ በላይ መድረሱን ጠቁሟል።

ፕሮጀክቱ ትውልዱ በቅብብሎሽ ሲዘክረው የሚኖር በድህነት ላይ የተከፈተ 2ኛው የአድዋ ድል ገጽ ያለው ዘመቻ ነውም ብሏል በመልዕክቱ።

ያላሰለሰ የኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በሁለንተናዊ ተሳትፎ መስዋ”ትነት የተከፈለበት እንደሆነም ተመላክቷል።

ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ እንዳትለማ የቅርብ እና ሩቅ ጠላቶች ለዘመናት ጥረት ቢያደርጉም በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ የጋራ ርብርብ የተፋሰስ ሀገራቱን የስምምነት ማዕቀፍ በማጽደቅ በቀጣናው የክፍለ ዘመኑን ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል ነው ያለው ጽህፈት ቤቱ።

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መላው ኢትዮጵያ ህዝብን ብሎም የተፋሰሱ ሀገራትን ህዝቦች በጋራ የማደግ ፍላጎት ጥላ ስር ያሰባሰበ፣ በቀጣናው የይቻላልን መንፈስ በተግባር ያረጋገጠ በድህነት ላይ የተጎናጸፍነው ዳግም ዓድዋ ድል እንደሚያደርገው አመልክቷል።

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ፕሮጀክቱ በዜጎች እና መንግስት የነቃ ተሳትፎ ቅብብሎሽ የማጠቃለያ ምዕራፍ ላይ በመድረሱ የሚያኮራ መሆኑንም ነው የገለጸው።

ጽህፈት ቤቱ ህዝቡ ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርቧል።

በህዝባዊ ተሳትፎና በጀግንነት የጀመርነውን ግድብ በአርበኝነት እናጠናቅቀዋለን ነው ያለው በመልዕክቱ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026