
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ ስምምነቱ ገቢራዊነት በቁርጠኝነት እንደምትሰራ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ።
ለሁለት ቀናት በጅቡቲ የተካሄደው የኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን ምስረታ የሚኒስትሮች መድረክ የጅቡቲ-ኢትዮጵያ-ደቡብ ሱዳን-ዩጋንዳ (DESSU) ኮሪደር ባለስልጣን መመስረቻ የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም ትናንት ማምሻውን ተጠናቋል።

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ታሪካዊው ስምምነት በአፍሪካ ቀንድ እና ምስራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ ንግድ፣ ትስስር እና ኢኮኖሚያዊ ትብብርን እንደሚያጠናክር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለስምምነቱ ትግበራ በቁርጠኝነት እንደምትሰራ እና በኮሪደሩ አማካኝነት የጋራ ብልጽግናን እውን እንዲሆን የበኩሏን ድርሻ እንደምትወጣም አረጋግጠዋል።
በስምምነቱ አማካኝነት ቀልጣፋ የሎጂስቲክስ አገልግሎት፣ ትብብሩ እንዲጠናከር እና ለሀገራቱ መጻዒ ጊዜው ብሩህ እንዲሆን የሚያስችል መንገድ ከፍተናል ብለዋል ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026