
ባህር ዳር፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፡-የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የአማራ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባህርዳር ከተማ እየተከናወነ የሚገኘውን የኮሪደር ልማት ጎበኙ።
ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ የጎበኙት በከተማው ከድሮው ጊዮን ሆቴል እስከ አጅፕ በመጀመሪያ ምዕራፍ የተገነባውን የኮሪደር ልማት ነው።
የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው፤ በከተማው 22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለመስራት ታቅዶ የመጀመሪያው ምዕራፍ 3 ኪሎ ሜትር እየተጠናቀቀ መሆኑ ተናግረዋል።
የስራ ኃላፊዎቹ ከኮሪደር ልማት ስራው በተጨማሪም በከተማዋ እየተገነቡ የሚገኙ ሌሎች የልማት ስራዎችን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጉብኝቱ ላይ በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የከተማ ዘርፍ አስተባባሪና የአማራ ክልል ከተሞችና መሰሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር)፤ የጉሙሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026