
ሮቤ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦ የሲኮ መንዶ የአርሶ አደሮች ህብረት ሥራ ዩኒየን ለ2017/18 የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን ገለጸ።
የዩኒየኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ታዬ እንደገለጹት፥ ዩኒየኑ ለዘንድሮው የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው።
ዩኒየኑ በእስካሁኑ ሂደት ካቀረበው ከ100 ሺህ በላይ የአፈር ማዳበሪያ 50 በመቶ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አመልክቷል።
በተለይም ዩኒየኑ ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ችግር በመቅረፍ በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች የተሻለ የሥርጭት ሂደት መመዝገቡን ተናግረዋል።
የአፈር ማዳበሪያውን ወደ ዞኑ የማጓጓዝ ስራው በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን በየቀኑ 25 መኪና የአፈር ማዳበሪያ ወደ ዩኒየኑ መጋዘን እንደሚገባም አረጋግጠዋል።

ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ከ100 ሺህ ሊትር የሚበልጡ የተለያዩ አይነት ኬሚካሎችን ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
የዞኑ የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ ደበሌ ሀቤቤ በበኩላቸው፥ በዞኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል።
በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የሚከናወኑ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ 3 ዩኒየኖችና 34 የህብረት ሥራ ማህበራት በማዳበሪያና ሌሎች የግብርና ግብዓቶች ስርጭት ላይ እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026