የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ዩኒየኑ ለበልግ የምርት ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ሮቤ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦ የሲኮ መንዶ የአርሶ አደሮች ህብረት ሥራ ዩኒየን ለ2017/18 የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ መሆኑን ገለጸ።

የዩኒየኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ታዬ እንደገለጹት፥ ዩኒየኑ ለዘንድሮው የበልግ ወቅት የሚውል 540 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ እያቀረበ ነው።

ዩኒየኑ በእስካሁኑ ሂደት ካቀረበው ከ100 ሺህ በላይ የአፈር ማዳበሪያ 50 በመቶ የሚሆነው ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን አመልክቷል።

በተለይም ዩኒየኑ ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት ችግር በመቅረፍ በተከናወኑ የማሻሻያ ስራዎች የተሻለ የሥርጭት ሂደት መመዝገቡን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውን ወደ ዞኑ የማጓጓዝ ስራው በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ሲሆን በየቀኑ 25 መኪና የአፈር ማዳበሪያ ወደ ዩኒየኑ መጋዘን እንደሚገባም አረጋግጠዋል።


ዩኒየኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ከ100 ሺህ ሊትር የሚበልጡ የተለያዩ አይነት ኬሚካሎችን ለማቅረብ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የዞኑ የህብረት ሥራ ማህበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ ደበሌ ሀቤቤ በበኩላቸው፥ በዞኑ የአርሶ አደሩን የማምረት አቅም የሚጨምሩ ግብዓቶችን በወቅቱ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ገልፀዋል።

በዞኑ ምርትና ምርታማነትን በመጨመር በምግብ ራስን ለመቻል የሚከናወኑ ተግባራትን ከዳር ለማድረስ 3 ዩኒየኖችና 34 የህብረት ሥራ ማህበራት በማዳበሪያና ሌሎች የግብርና ግብዓቶች ስርጭት ላይ እየሰሩ መሆኑንም አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026