
ደብረብርሀን፤ የካቲት 15ቀን 2017(ኢዜአ) አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በደብረብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና በፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።
የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ ዋን ወይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ፋብሪካንና ጅንሹ ኢትዮጵያ የቴክስታይል ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።
አቶ አብርሃም ማርሻሎ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ስራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።
በተለይም በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ የአካባቢውን የቱሪዝም ልማት ለማሳደግና ለስራ እድል ፈጠራ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
የደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፥ በከተማዋ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የንግድና የኢንቨስትመንት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ባለፉት ሰባት ወራት 17 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፥ የተካሄደው ጉብኝትም ከከፍተኛ አመራሮች በሚገኝ ግብዓት በቀጣይ የላቀ ልማት ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026