የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው</p>

Feb 24, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሀን፤ የካቲት 15ቀን 2017(ኢዜአ) አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በደብረብርሀን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የኢንቨስትመንት ተግባራት የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት መገለጫ ናቸው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና በፓርቲው የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ገለጹ።


የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በደብረ ብርሀን ከተማ የሚገኙ ዋን ወይ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ፋብሪካንና ጅንሹ ኢትዮጵያ የቴክስታይል ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።


አቶ አብርሃም ማርሻሎ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ በደብረ ብርሀን ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢንቨስትመንት ስራዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ ናቸው።


በተለይም በከተማዋ እየተከናወነ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ የአካባቢውን የቱሪዝም ልማት ለማሳደግና ለስራ እድል ፈጠራ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ነው ብለዋል።


የደብረ ብርሀን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት በበኩላቸው፥ በከተማዋ ሰላምን ከማጽናት ጎን ለጎን የንግድና የኢንቨስትመንት ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።


ባለፉት ሰባት ወራት 17 ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት መሸጋገራቸውን ጠቁመው፥ የተካሄደው ጉብኝትም ከከፍተኛ አመራሮች በሚገኝ ግብዓት በቀጣይ የላቀ ልማት ለማከናወን ያግዘናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026