
ወላይታ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፡- ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) አስገነዘቡ።
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ 524 ተማሪዎች ዛሬ አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና(ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እንደ ሀገር ብልጽግናን ለማረጋገጥና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመሩ ሥራዎችን ለማጠናከር በየመስኩ ብቁ የሰለጠነ የሰው ሀይል ያስፈልጋል።
በመሆኑም ምሩቃን በሰለጠኑበት ሙያ ምርምር በማድረግና በአዳዲስ እሳቤዎች የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጠንክረው እንዲሰሩ አስገንዝበዋል።
በተለይ የአርሶ አደሩን ባህላዊ የአመራረት ዘይቤ በመቀየር ውጤታማ ለማድረግ በቅርበት ሆነው መስራት እንዳለባቸውም አመልክትዋል።
ሀገር ወደ ተሻለ ደረጃ እንድትደርስ የመቻቻል፣ የመደጋገፍና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበትና ሙስናን የሚጸየፍ ትውልድ ለመፍጠር የበኩላቸውን እንዲወጡም አሳስበዋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ጉቼ ጉሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ መስኮች በዕውቀትና በክህሎት የሰለጠነ የሰው ሀይል እያፈራ መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ምርምሮች እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራዎችን ማከናወኑንም ገልጸዋል።
የዛሬ ተመራቂዎችም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀትና ክህሎት ተጠቅመው በቀጣይ ህዝባቸውንና ሀገራቸውን በቅንነት እንዲያገለግሉ ጠይቀዋል።
በሦስተኛ ዲግሪ የተመረቁት ተገኝ ሀይሉ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ባገኙት እውቀት ሀገርና ህዝብን ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከዛሬ ምሩቃን መካከል 737ቱ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በወላይታ ሶዶና ታርጫ ካምፓሶች በመደበኛ፣ በማታ፣ በእረፍት ቀናትና በርቀት የትምህርት መርሀግብሮች 39 ሺህ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ መሆኑን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026