
አዲስ አበባ፤ የካቲት 13/2017(ኢዜአ)፡- የአፍሪካ ልህቀት አካዳሚ ከሸገር ከተማ አስተዳደር፣ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችለውን የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ።
ስምምነቱን የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ፣ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እንዲሁም የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ ፈርመዋል።

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት አቶ ዛዲግ አብርሃ አካዳሚው በዛሬው እለት ከሶስት ተቋማት ጋር በትብብር መስራት የሚያስችሉትን ስምምነቶች መፈራረሙን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የእድገት ግስጋሴ እውን እንዲሆን የዘመኑ ከተሞችን መገንባትና ማልማት እንዲሁም ከተሞችን የሚመሩ አመራሮችን አቅም ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
ለዚህም አካዳሚው የሸገር ከተማ አስተዳደር አመራሮችን አቅም ለማጎልበት እና ሌሎች ተያያዥ ተግባራትን ለማከናወን እንደሚሰራም ጠቁመዋል።

በተመሳሳይ ወጣቶችን በአመራርነት ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት እና ከፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ጋር በትብብር ይሰራል ብለዋል።
የሸገር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ተሾመ አዱኛ(ዶ/ር) የከተማዋን እድገት በማፋጠን ተወዳዳሪ ብሎም ለማህበረሰቡ ቀልጣፋ እና የዘመነ አገልግሎትን መስጠት የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
ነገር ግን ከተማዋን ለማዘመን በተወሰነ አካል ብቻ በሚሰራ ስራ የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት አዳጋች መሆኑን ገልጸው ከተለያዩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት ይጠይቃል ብለዋል።
በተለይም አንድን ከተማ እውቀትን በአግባቡ በመጠቀም ማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን የሚጠይቅ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም በጥናትና ምርምር እንዲሁም በስልጠና ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር በትብብር መስራት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
ይህን መነሻ በማድረግ የከተማ አስተዳደሩ የአቅም ግንባታና ሌሎች ለከተማው የሚጠቅሙ ስራዎችን ከአካዳሚው ጋር ለመስራት ስምምነቱ መፈረሙን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ፉአድ ገና እና የፓን አፍሪካ ወጣቶች ህብረት ዋና ፀሐፊ ዊዚቾንግ ቤኒንግ አህመድ በበኩላቸው የወጣቶችን የአመራርነት አቅም ለመገንባትና ሌሎች ከወጣቶች ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ስምምነቱ ትልቅ ጠቀሜታ እንደሚያበረክት ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026