
መቱ፤ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል የጤና አገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ የማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን የክልሉ ጤና ቢሮ ገለጸ።
የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶክተር ቦኮና ጉታ እንደተናገሩት፥ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ ነው።
ከተጀመሩ ጥረቶች መካከል በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ማድረግ ተጀምሯል ብለዋል።
በዚህ ዓመትም በክልሉ በአስር ሆስፒታሎችና በአምስት ጤና ጣቢያዎች ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት ተግባራዊ ተደርጓል ነው ያሉት።
በቀጣይም በክልሉ በሁሉም የጤና ተቋማት ከወረቀት ነጻ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ የተጀመረው ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ከወረቀት ነጻ የሕክምና አገልግሎት መስጠት ከተጀመረባቸው ተቋማት መካከል የመቱ ኮምፕሬንሲቭ ስፔሻላይዝድ ካርል ሆስፒታል አንዱ ነው።
የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሶላን በቀለ፤ በአሁኑ ወቅት በሆስፒታሉ እየተሰጠ የሚገኘው የሕክምና አገልግሎት ከወረቀት ነጻ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ለተገልጋዩ የተቀላጠፈ የሕክምና አገልግሎት መስጠት እያስቻለ ሲሆን ከዚህ በፊት ሲነሱ የነበሩ ቅሬታዎችም መቀነሳቸውን ተናግረዋል።
የመቱ ሆስፒታል ከወረቀት ነጻ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን በጤና ሚኒስቴር አመራሮችና በክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮች ተጎብኝቷል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026