
አዲስ አበባ፤የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮ በኢትዮጵያ መከፈቱ በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶች ላይ ያላትን የነቃ ተሳትፎ የሚያሳይ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት(ተመድ) የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መክፈቱን ዛሬ ይፋ አድርጓል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)፣ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)፣ የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጄፍሪ ሳክስ እና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት በዓለም ዙሪያ ያሉ የፈጠራ ልሂቃንና የቴክኒክ ባለሙያዎችን የሚያሰባስብ ነው፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚህ ወቅት እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ሁሉን አቀፍ ሪፎርም አድርጋለች፡፡
የኢትዮጵያ የ10 ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ ዘላቂ ልማትን የሚያረጋግጥ መዳረሻውን ብልጽግና ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች አካታች ሪፎርም መደረጉን ገልጸው፥ ኢትዮጵያ የዘላቂ የልማት ግቦችን በማሳካት የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቧን ጠቅሰዋል፡፡
በምሥራቅ አፍሪካ ትልቅ ህዝብና ኢኮኖሚ የላት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው፥ በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት ምስረታና አበርክቶ የጎላ ሚና እንዳላትም ገልጸዋል፡፡
የተመድ የዘላቂ ልማት መፍትሔ ጥምረት የአፍሪካ ቢሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መከፈትም ኢትዮጵያ በቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁነቶች ያላትን የነቃ ተሳትፎ የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ በሚያስችል ቁመና ላይ የተመሰረተ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ ግቡን ለማሳካት የተለያዩ የፖሊሲ ርምጃዎች ተወስደዋል ብለዋል፡፡
የውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማዘመን፣ኢንቨስትመንትን ማሳደግ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ማሻሻል ትኩረት የተደረገባቸው እንደሆኑም ገልጸዋል፡፡
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ ግብርና ቱሪዝምና ማዕድን የመንግስት የትኩረት መስኮች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የመንግስት የዲጂታል አገልግሎትና ዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ እምርታዊ ለውጥ ማስመዝገቡን ተናግረዋል፡፡
መንግሥት የኢንዱስትሪ ፓርኮችን በማስፋፋትና የተሟላ መሰረተ ልማት በማቅረብ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ እንዲያድግ ማድረጉንም ተናግረዋል፡፡
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026