
አዲስ አበባ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- የናይጀሪያው ኩባንያ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የሲሚንቶ የማምረት አቅሙን በዕጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን ገለፀ።
ኩባንያው በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ለመሰማራትም ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል።
የዳንጎቴ ግሩፕ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ጋር በኩባንያው ኢንቨስትመንት ማሻሻያ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

አሊኮ ዳንጎቴ በማብራሪያቸው እንዳሉት የኢትዮጵያ መልክዓ ምድርና የአየር ሁኔታን ጨምሮ ያሉ ምቹ ሁኔታዎችለየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሠማራት ምቹ ሀገር ናት።
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንታቸውን ለማስፋፋት አማራጮችን እየቃኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዛሬው ዕለትም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በኢንቨስትመንት ነክ ጉዳዮች መወያየታቸውን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ሪፎርም በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያነሳሳ እንደሆነም ጠቁመዋል።
ቀደም ብሎ በሲሚንቶ ኢንቨስመንት የተሰራማራው ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ምቹ የኢንቨስመንት ከባቢ በማየት ምርቱን በዕጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን አብስረዋል።
በዚህም በአመት 2 ነጥብ 5 ሚሊዬን ቶን ሲሚንቶ የማመረትን አቅም ወደ አምስት ሚሊዬን ቶን እንደሚያሳድገው አብራርተዋል።

ከሲሚንቶ ባሻገርም በኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በሚያሳድጉ ዘርፎች ለአብነትም በአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመክፈት እቅድ መያዙንም አንስተዋል።
በስኳር ልማት ያለውን ልምድ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት በኦሞ ኩራዝ የማስፋፊያ ስራ እንደሚያከናውን ለአብነት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰቱን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።
ለውጪ ሀገር አልሚዎች በተፈጠረው ልዩ ዕድል በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎታቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው፤ ዳንጎቴ ግሩፕ ለዚህ ሁነኛ ማሳያ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026