የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ምርቱን በዕጥፍ ሊያሳድግ ነው</p>

Feb 17, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- የናይጀሪያው ኩባንያ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የሲሚንቶ የማምረት አቅሙን በዕጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን ገለፀ።

ኩባንያው በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ለመሰማራትም ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል።

የዳንጎቴ ግሩፕ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ጋር በኩባንያው ኢንቨስትመንት ማሻሻያ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።


አሊኮ ዳንጎቴ በማብራሪያቸው እንዳሉት የኢትዮጵያ መልክዓ ምድርና የአየር ሁኔታን ጨምሮ ያሉ ምቹ ሁኔታዎችለየትኛውም የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሠማራት ምቹ ሀገር ናት።

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንታቸውን ለማስፋፋት አማራጮችን እየቃኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዛሬው ዕለትም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በኢንቨስትመንት ነክ ጉዳዮች መወያየታቸውን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ሪፎርም በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያነሳሳ እንደሆነም ጠቁመዋል።

ቀደም ብሎ በሲሚንቶ ኢንቨስመንት የተሰራማራው ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የተፈጠረውን ምቹ የኢንቨስመንት ከባቢ በማየት ምርቱን በዕጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን አብስረዋል።

በዚህም በአመት 2 ነጥብ 5 ሚሊዬን ቶን ሲሚንቶ የማመረትን አቅም ወደ አምስት ሚሊዬን ቶን እንደሚያሳድገው አብራርተዋል።


ከሲሚንቶ ባሻገርም በኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በሚያሳድጉ ዘርፎች ለአብነትም በአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመክፈት እቅድ መያዙንም አንስተዋል።

በስኳር ልማት ያለውን ልምድ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት በኦሞ ኩራዝ የማስፋፊያ ስራ እንደሚያከናውን ለአብነት ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፍሰቱን ለማሳደግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።

ለውጪ ሀገር አልሚዎች በተፈጠረው ልዩ ዕድል በተለያዩ ዘርፎች ለመሰማራት ፍላጎታቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው፤ ዳንጎቴ ግሩፕ ለዚህ ሁነኛ ማሳያ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026