
ወልድያ፤ የካቲት 8/2017 (ኢዜአ)፡- በሰሜን ወሎ ዞን በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ሰባት ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የዞኑ እንስሳትና አሳ ሃብት ልማት ተጠሪ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የሰሜን ወሎ ዞን የሌማት ቱሩፋት ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ በስታይሽ ከተማ ዛሬ ተካሂዷል።

የተጠሪ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ነጋ ጌታቸው፣ በውይይቱ ላይ እንዳሉት የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር በስራ እድል ፈጠራ፣ በገበያ ማረጋጋትና የስራ ባህል በመቀየር አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በዚህም በዞኑ የሚገኙ ሰባት ሺህ የሚጠጉ ወጣቶችን በእንስሳት እርባታና ማድለብ፣ በንብ ማነብና በአትክልትና ፍራፍሬ ልማት ስራ በማሳተፍ ተጠቃሚነታቸውን እንዲያረጋግጡ መደረጉን ገልጸዋል።
በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ስጋ፣ እንቁላልና አትክልትና ፍራፍሬ ለገበያ በማቅረብ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በአሳ እርባታ የተሻሉ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው በዘርፉ ወጣቶችን በአሳ ልማት በማሰማራት አሁን ላይ ለገበያ የአሳ ምርት ማቅረብ መጀመራቸውን ሀላፊው ጠቅሰዋል።
የሰሜን ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ታምራት ንጋቱ፤ በዞኑ የሌማት ቱርፋት ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ አበረታች ለውጦች እየተገኙ ነው።

ዘርፉ ከምግብ አቅርቦት ባለፈ የስራ እድል በመፍጠር የወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የስራ እድል ከመፍጠር ባሻገር በምግብ ራስን ለመቻልና ህብረተሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።
የዛሬው ውይይትም በዘርፉ አፈጻጸም ላይ የታዩ ጥንካሬዎችን ለማስቀጠልና ክፍተቶችን በማረም ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ መድረክ መሆኑን አስረድተዋል።
በውይይት መድረኩ ላይም የሰሜን ወሎ ዞን የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026