
ቡታጅራ፣ የካቲት 7/2017 (ኢዜአ)፡-የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን የሚገመግም መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ መካሄድ ጀመረ።
"በጥራት ወደ ተሳለጠ የንግድ ስርዓት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ መድረክ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የክልልና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች የንግድ ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በጉባኤው የሚኒስቴሩ የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት የሚካሄድበት ሲሆን ለቀጣይ የሥራ አቅጣጫም እንደሚቀመጥ ተገልጿል።
በተጨማሪም የሁሉም ክልሎች የሴክተር ቢሮዎች የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ የሚገመገም ሲሆን የንግድ ተቋማት የሥራ እንቅስቃሴ ላይም ምልከታ ይደረጋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026