
አዲስ አበባ፤ የካቲት 05/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን ለመመስረት ሲካሄድ የነበረው የውይይት መድረክ ዛሬ በስምምነት ተጠናቋል።
የኢትዮ-ጅቡቲ ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን ለመመስረት የሚያስችል ጉዳዮች ላይ በሁለቱ ሀገራት የጋራ የቴክኒክ ኮሚቴ ደረጃ ሰፊ ውይይት ሲደረግ ቆይቷል።
በውይይቱም የሁለትዮሽ ረቂቅ የመመስረቻ ሰነድ ላይ የተለያዩ ግብዓቶችን በመጨመር በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጠናቆ ለፊርማ ዝግጁ እንዲሆን ከስምምነት ላይ ተደርሷል።

ላለፉት ሁለት ቀናት የተደረገው ውይይት በጋራ ለመስራት በተስሟሟቸው አጀንዳዎች ዙሪያ በመፈራረም እና የጋራ መግለጫ በመስጠት መጠናቀቁን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያመረጃ ያሳያል።
በመድረኩ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የጅቡቲ መሰረተ-ልማት እና ኢኪዩፕመንት ሚኒስትር ሀሰን ሀሙድ፣ የጅቡቲ ንግድ እና ቱሪዝም ሚኒስትር መሀመድ ዋርሳማ እና ሌሎች የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...
Apr 8, 2026
ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...
Apr 8, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026