የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት መረጋገጥና የንግድ ልውውጥ ማደግ አበክራ እየሰራች ነው - ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)</p>

Feb 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 5/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት መረጋገጥና የንግድ ልውውጥ ማደግ አበክራ እየሰራች መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

"ከቪዛ- ነጻ እንቅስቃሴ ለአፍሪካ ትራንስፎርሜሽን" በሚል መሪ ሃሳብ የአፍሪካ ሚኒስትሮች ስትራቴጂካዊ ምክክር መድረክ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) የአፍሪካ ህብረትና የአፍሪካ ልማት ባንክ አመራሮች እንዲሁም ከተለያዩ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሀገራት የንግድ ትስስር እንዲጠናከር በርካታ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች፡፡


እንዲሁም ገበያዎቿን ለአፍሪካ ሀገራት ክፍት በማድረግ በሀገራት መካከል ያለው የንግድ ትስስር እንዲጠናከር በትኩረት እየሰራች እንደምትገኝም ነው ያነሱት፡፡

ኢትዮጵያ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለአህጉራዊ የንግድ ትስስር መሳለጥ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ላይ ናትም ብለዋል።

በአፍሪካ ነጻ የንግድ ቀጣና የሙከራ ንግድ ለመጀመር ዝግጅቷን ማጠናቀቋም በአህጉሪቱ ያለው የንግድ ልውውጥ የተቀላጠፈ እንዲሆን ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ አፍሪካውያን ከቅኝ ግዛት ነጻ እንዲወጡ በፓንአፍሪካዊ እሳቤ ታሪካዊ ሚና መወጣቷን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ በዚህም የአፍሪካውያን የነጻነት ቀንዲል ሆናለች ብለዋል።

አፍሪካውያን በዚህ ዘመን የእርስ በርስ ትስስራቸው እንዲጎለብት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታቸውን እንዲያረጋግጡና በአህጉሪቱ የንግድ ልውውጥ እንዲጠናከር ታሪካዊ ሚናዋን እየተወጣች መሆኑንም ገልጸዋል።


በአፍሪካ ህብረት የሠራተኞች፣ የሥራ ቅጥርና የስደተኞች ዘርፍ ኃላፊ ሳቤሎ ምቦካዚ(ዶ/ር) በበኩላቸው፥ የአፍሪካውያን ከቪዛ ነጻ ዝውውር እውን መሆን አፍሪካ ላሰበችው የነጻ ቀጣና ኢኮኖሚ ትስስር ትልቅ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

ህብረቱ ከቪዛ ነጻ እንቅስቃሴን እንዲያጠናክሩ በትኩረት እንደሚሠራም አረጋግጠዋል።


የአፍሪካ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት ኒና ንዋቡፎ፥ አፍሪካ በተፈለገው ደረጃ የነጻ ቪዛ እንቅስቃሴን መተግበር አለመቻሏ ኢኮኖሚዋ እንዳያድግ ማነቆ መሆኑን አንስተዋል።

በመሆኑም ከቪዛ ነጻ እንቅስቃሴን በመፍቀድ አህጉራዊ ኢኮኖሚንና የንግድ እንቅስቃሴን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ እንደሚቻል ነው የጠቆሙት።

ከቪዛ ነጻ እንቅስቃሴ የአፍሪካ ኢኮኖሚን በከፍተኛ ሁኔታ ከማሳደጉ በተጨማሪ የስራ እድልን የሚያሰፋ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ አባል ሀገራት በቁርጠኝነት መስራት እንዳለባቸው ተመላክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ቀጣናዊ ደኅንነትን በማስጠበቅ ለጋራ ብልፅግና ወሳኝ ነው

አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ምላሽ ማግኘት ከሀገራዊ ጥቅም ባለፈ ለዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ደህንነትን ...

Apr 8, 2026

የለውጥ ጉዟችንን ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል ነው

ዲላ ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ)፦የለውጥ ዓመታቱን ጉዞ ስንዘክር ያስመዘገብናቸውን ስኬቶች በማስቀጠል መሆን አለበት ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ር...

Apr 8, 2026

የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...

Mar 27, 2026

የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ የኢንቨስትመንት ማዕከልነት እያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...

Mar 26, 2026